ጉረኞች፣
ትዕቢተኞች፣ ተሳዳቢዎች
በመጨረሻዎቹ ቀናት ለመቋቋም የሚያስቸግር በዓይነቱ ልዩ የሆነ ዘመን እንደሚመጣ ይህን እወቅ። ምክንያቱም ሰዎች ራሳቸውን የሚወዱ፣ ገንዘብ የሚወዱ፣ ጉረኞች፣ ትዕቢተኞች፣ ተሳዳቢዎች፣ ለወላጆቻቸው የማይታዘዙ፣ የማያመሰግኑ፣ ታማኝ ያልሆኑ፣ ተፈጥሯዊ ፍቅር የሌላቸው፣ ለመስማማት ፈቃደኞች ያልሆኑ፣ ስም አጥፊዎች፣ ራሳቸውን የማይገዙ፣ ጨካኞች፣ ጥሩ ነገር የማይወዱ፣ ከዳተኞች፣ ግትሮች፣ በኩራት የተወጠሩ፣ ከአምላክ ይልቅ ሥጋዊ ደስታን የሚወዱ ይሆናሉ፤ ለአምላክ ያደሩ መስለው ይታያሉ፤ በሥራቸው ግን ኃይሉን ይክዳሉ።”2 ጢሞ. 3:1-5
መጽሐፍ ቅዱስ ከላይ የተጠቀስውን ህሳቤ እያስተማረ እያለ፣በዛሬው ጊዜ ብዙ ሰዎች ጉረኝነትን እንደ ጥሩ ነገር አድርገው ይዘውታል። ጠንካራ ጎኔ፣ ችሎታዬና ያከናወንኩት ጥሩ ሥራ ይታይልኝ ማለት የተለመደ እየሆነ መጥቷል። አንዳንዶች አሸናፊ ለመሆን ጉራ መንዛት ያስፈልጋል ብለው ያምናሉ። ጉረኝነት የአንድን ሰው ክብር ከፍ እንደሚያደርግ የሚሰማቸውም አልታጡም። ታይም መጽሔት “ትሕትና ጊዜ ያለፈበት እየሆነ መጥቷል” ሲል ጽፏል። ጁዲ ጌሊን የተባሉ ደራሲ እንደሚከተለው ብለዋል:- “የሚያሳዝነው ግን ያለምንም እፍረት ጉራ መንዛት . . . አዲስ ፋሽን ሆኗል። ከጓደኛ ወይም ከሚያውቁት ሰው ጋር በሚደረገው ጭውውት ውስጥ ጉራ መንፋት እንደ ቅመም ይጨመራል።”
መጽሐፍ ቅዱስ ከላይ የተጠቀስውን ህሳቤ እያስተማረ እያለ፣በዛሬው ጊዜ ብዙ ሰዎች ጉረኝነትን እንደ ጥሩ ነገር አድርገው ይዘውታል። ጠንካራ ጎኔ፣ ችሎታዬና ያከናወንኩት ጥሩ ሥራ ይታይልኝ ማለት የተለመደ እየሆነ መጥቷል። አንዳንዶች አሸናፊ ለመሆን ጉራ መንዛት ያስፈልጋል ብለው ያምናሉ። ጉረኝነት የአንድን ሰው ክብር ከፍ እንደሚያደርግ የሚሰማቸውም አልታጡም። ታይም መጽሔት “ትሕትና ጊዜ ያለፈበት እየሆነ መጥቷል” ሲል ጽፏል። ጁዲ ጌሊን የተባሉ ደራሲ እንደሚከተለው ብለዋል:- “የሚያሳዝነው ግን ያለምንም እፍረት ጉራ መንዛት . . . አዲስ ፋሽን ሆኗል። ከጓደኛ ወይም ከሚያውቁት ሰው ጋር በሚደረገው ጭውውት ውስጥ ጉራ መንፋት እንደ ቅመም ይጨመራል።”
ብዙዎች ተደናቂ የሆኑ ሰዎችን እንደ አርአያ አድርገው
በመመልከት
የሚያደርጉትን
ሁሉ
ይቀዳሉ።
“በዚህ
የታሪክ
ወቅት
ላይ
የእኔ
በዓለም
ላይ
ታላቅ
ሰው
መሆን
እንዲሁ
በአጋጣሚ
የመጣ
አይደለም”
ሲል
አንድ
የቀድሞ
የቦክስ
ሻምፒዮና
የተናገራቸውን
ቃላት
ሰምተህ
ይሆናል።
የቢትልስ
የሙዚቃ
ባንድ
አባል
የሆነ
አንድ
ሰው
“በአሁኑ
ጊዜ
እኛ
ከኢየሱስ
ክርስቶስ
የበለጠ
ተወዳጅነት
አለን”
ሲል
የተናገረው
የታወቀ
አባባልም
አለ።
አንዳንዶች
እነዚህን
አባባሎች
ክፋት
እንደሌለባቸው
አድርገው
ቢመለከቷቸውም
ሌሎች
ግን
ራስን
ከፍ
ከፍ
ማድርግ
ተገቢ
መሆኑን
የሚያሳዩ
ጥሩ
ምሳሌዎች
እንደሆኑ
አድርገው
በመመልከት
እነዚህን
ቃላት
የተናገሩትን
ሰዎች
ይከተላሉ።
የጉረኝነት
መብዛት
የሚከተለውን
ጥያቄ
ያስነሣል:-
አንድ
ሰው
ስለ
ንብረቱና
ስለ
ችሎታው
ጉራውን
ቢነዛ
ትክክል
ነውን?
አንድ
ሰው
በሥራው
ውጤት
ኩራት
ቢሰማውና
ይህንንም
ለቅርብ
ጓደኞቹና
ለዘመዶቹ
ቢነግር
ምንም
ስሕተት
የለበትም።
ይሁን
እንጂ
“አንድ
ዓይነት
ሀብት
ወይም
ችሎታ
ካለህ
በሌሎች
ዘንድ
እንዲታይልህ
አድርግ”
በሚለው
አባባል
ስለሚስማሙት
ሰዎች
ምን
ሊባል
ይቻላል?
በተጨማሪም
በግልጽ
ጉራቸውን
ባይነዙም
በተዘዋዋሪ
ግን
ስለችሎታቸውና
ስላከናወኑት
ሥራ
ሌሎች
እንዲያውቁላቸው
ለማድረግ
ስለሚጥሩትስ?
አንዳንዶች
እንደሚሉት
እንዲህ
ዓይነቱ
ልታወቅ
ልታወቅ
ባይነት
ትክክል
ወይም
አስፈላጊ
ነውን?
ሰዎች ጉራ መንዛታቸው
በአንተ
ላይ
የሚኖረውን
ተጽዕኖ
አስብ።
ለምሳሌ
ቀጥሎ
ያሉትን
አነጋገሮች
እንዴት
ትመለከታቸዋለህ?
“ሌሎች ሰዎች ከጻፏቸው
መጽሐፎች
ይልቅ
እኔ
ያልጻፍኳቸው
መጽሐፎች
ይበልጣሉ።”
— አንድ
የታወቁ
ደራሲ።
“በፍጥረት
ጊዜ ኖሬ
ቢሆን ኖሮ
አጽናፈ ዓለም የተሻለ
አቀማመጥ እንዲኖረው ጠቃሚ
ምክር እሰጥ
ነበር።” - አንድ የመካከለኛው
ዘመን ንጉሥ።
“አምላክ ሊኖር
አይችልም፤ ምክንያቱም አምላክ
ካለ ከኔ
በቀር ሌላ
ሊሆን አይችልም።”
— አንድ የ19ኛው መቶ
ዘመን ፈላስፋ። በዚህ አነጋገራቸው
እነዚህ ሰዎች ይማርኩሃልን?
አብረሃቸው ብትሆን የምትደሰት
ይመስልሃልን? እንደማትደሰት የተረጋገጠ
ነው። በቅንነትም
ሆነ በቀልድ
የሚነገር ጉራ ሌሎች
እንዲጨነቁ፣ እንዲናደዱ፣ ምናልባትም
ቅንዓት እንዲያድርባቸው ያደርጋል።
በመዝሙራዊው አሳፍ ላይ
ያሳደረው ተጽዕኖ ይህ
ነበር። እሱም “የኃጢአተኞችን
ሰላም አይቼ
በዓመጸኞች ቀንቼ ነበርና”
ሲል ሳይሸሽግ
ተናግሯል። (መዝሙር 73:3)
ማናችንም ብንሆን በወዳጆቻችንና
አብረውን በሚውሉ ሰዎች
ላይ መጥፎ
ስሜት ማሳደር
እንደማንፈልግ የተረጋገጠ ነው።
አንደኛ ቆሮንቶስ 13:4
“ፍቅር . . . አይመካም” ይላል።
አምላካዊ የሆነ ፍቅርና
ለሌሎች ስሜት ያለን
አሳቢነት ችሎታችንና ሀብታችን
ይታይልን ከማለት እንድንቆጠብ
ይገፋፋናል።
አንድ ሰው
ራሱን የሚቆጣጠርና
የማይመካ ከሆነ አጠገቡ
ያሉት ሰዎች
እንዲዝናኑና ስለራሳቸው ጥሩ
ስሜት እንዲኖራቸው
ያደርጋል። ይህ ደግሞ
እጅግ ውድ
የሆነ ችሎታ
ነው። እንግሊዛዊ
የፖለቲካ ሰው የነበሩት
ሎርድ ቼስተርፊልድ
“ከቻልክ ከሌሎች ሰዎች
የበለጠ ጥበበኛ ሁን፤
ነገር ግን
ከእነሱ የበለጠ ጥበበኛ
መሆንህን አትንገራቸው” ሲሉ
ልጃቸውን የመከሩት ምናልባት
ይህን በአእምሮአቸው
ይዘው ይሆናል።
የሰዎች ተሰጥዎ
ይለያያል። ለአንዱ ቀላል
የሆነው ለሌላው ከባድ
ሊሆን ይችላል።
አንድ ሰው
ፍቅር ካለው
የእሱ ዓይነት
ተሰጥዎ የሌላቸውን ሰዎች
በርኅራኄ እንዲይዝ ይገፋፋዋል።
ሌላው ሰው
ደግሞ በሌላ
መስክ የራሱ
ተሰጥዎ ሊኖረው ይችላል።
ሐዋርያው ጳውሎስ “እግዚአብሔር
ለእያንዳንዱ የእምነትን መጠን
እንዳካፈለው፣ እንደ ባለ
አእምሮ እንዲያስብ እንጂ
ማሰብ ከሚገባው
አልፎ በትዕቢት
እንዳያስብ በመካከላችሁ ላለው
ለእያንዳንዱ በተሰጠኝ ጸጋ
እናገራለሁ” ሲል መክሮናል።
ሮሜ
12:3
አንዳንድ ሰዎች
ከጉረኛ ሰዎች ጋር
በሚሆኑበት ጊዜ የበታችነት
ስለሚሰማቸው ከእነሱ ይርቃሉ።
ሌሎች ደግሞ
ከዚህ የተለየ
ግምት ይወስዳሉ።
ጉረኞች በራሳቸው የማይተማመኑ
ሰዎች ናቸው
ብለው ይደመድማሉ።
ፍራንክ ትሪፔት የተባሉት
ደራሲ ጉረኛ
ሰው በሌሎች
ዓይን ለምን
ዝቅ ብሎ
እንደሚታይ እንደሚከተለው በማለት
ያብራራሉ:- “ጉረኝነት ብዙውን
ጊዜ አንዳንድ
የግል ድክመቶችን
እንደሚያሳይ ማንም ሰው
በልቡ ያውቃል።”
ብዙ ሰዎች
የጉረኞች ውስጣዊ ሁኔታ
በቀላሉ ስለሚገባቸው ጉራ
ከመንዛት መቆጠብ ጥበብ
አይደለምን?
“ግን እኮ
ሊካድ አይችልም!”
አንዳንዶች ራስን
ከፍ ከፍ
ማድረግ ተገቢ እንደሆነ
ለማስመሰል የሚሰጡት ምክንያት
ይህ ነው።
በአንዳንድ ነገሮች በእርግጥ
ተሰጥዎ እያላቸው እንደሌላቸው
ሆኖ መታየት
ግብዝነት እንደሆነ ይሰማቸዋል። ይሁን
እንጂ ጉራቸው
እውነት ነውን? ለራስ
የሚሰጠው ግምት ከአድልዎ
የጸዳ አይሆንም።
እኛ ለራሳችን
እንደ ትልቅ
ችሎታ አድርገን
የምንገምተው ነገር በሌሎች
ዘንድ ተራ
ሊሆን ይችላል።
አንድ ሰው
ችሎታውን ማሳየት እንዳለበት
በኃይል ከተሰማው ችሎታው
ያን ያህል
እንዳልሆነ፤ የማስታወቂያ ድጋፍ
የሚያስፈልገው ደካማ ችሎታ
መሆኑን ያሳያል። መጽሐፍ
ቅዱስ “እንደ ቆመ
የሚመስለው እንዳይወድቅ ይጠንቀቅ”
የሚል ማስጠንቀቂያ
በመስጠት ራስን የማታለል
ሰብዓዊ ዝንባሌ እንዳለ
ይጠቁማል። 1 ቆሮንቶስ
10:12
አንድ ሰው
በአንድ ዓይነት መስክ
ልዩ ተሰጥዎ
ቢኖረውም እንኳ ይህ
ራሱ ጉራውን
እንዲነዛ ሊያደርገው ይገባልን?
አይገባም፤ ምክንያቱም ጉራ
መንዛት ሰውን ከፍ
ከፍ ያደርጋል፤
ነገር ግን
ያለን ማንኛውም
ተሰጥዎ ከአምላክ የመጣ
ነው። ክብር
ሊቀበል የሚገባው እርሱ
ነው። በተፈጥሮ
ላገኘነው ነገር ለምን
ክብር እንቀበላለን?
(1 ቆሮንቶስ 4:7)
ከዚህም በተጨማሪ ጠንካራ
ጎኖች እንዳሉን
ሁሉ ድክመቶችም
አሉን። ሐቀኝነት ስህተቶቻችንንና
ድክመቶቻችንን እንድናውቅ ያስገድደናልን?
እንዲህ ብለው የሚያስቡ
ጉረኞች የሉም ማለት
ይቻላል። ንጉሥ ሄሮድስ
አግሪጳ ግሩም የንግግር
ችሎታ ያለው
ሰው ኖሮ
ሊሆን ይችላል።
ይሁን እንጂ
ከትምክህተኝነት አለመራቁ መጥፎ
አሟሟት አስከትሎበታል። በሄሮድስ
ላይ የደረሰው
ይህ አስቀያሚ
ሁኔታ ትምክህተኝነት
በብዙ ሰዎች
ዘንድ የተጠላ
እንደሆነ ሁሉ በአምላክ
ዘንድም የቱን ያህል
የተጠላ እንደሆነ ያሳያል።
የሐዋ. ሥራ
12:21–23
ተሰጥዎቻችንና ጠንካራ
ጎኖቻችን ምንም ማስታወቂያ
ሳንናገር ራሳቸው መታወቃቸው
አይቀርም። ሌሎች ሰዎች
አንድ ሰው
ያለውን ችሎታ ወይም
ያከናወነውን ጥሩ ሥራ
ተመልክተው ሲያመሰግኑት ምስጋናውን
ለሚቀበለው ሰው የበለጠ
ሞገስ ይሆንለታል።
ምሳሌ 27:2
“ሌላ ያመስግንህ
እንጂ አፍህ
አይደለም፤ ባዕድ ሰው
እንጂ ከንፈርህ
አይደለም” በማለት የጥበብ
ምክር ይሰጣል።
አንዳንዶች ፉክክር
ባለበት በዛሬው ኅብረተሰብ
ውስጥ ተወዳዳሪን
ለማሸነፍ በትምክህት ራስን
ከፍ ከፍ
ማድረግ አስፈላጊ እንደሆነ
ይሰማቸዋል። ስለ ችሎታዎቻቸው
በይፋ ካልተናገሩና
እንታይ እንታይ ካላሉ
ሳይደነቁና ማንም ሳያውቃቸው
ተረስተው የሚቀሩ ስለሚመስላቸው
ይጨነቃሉ። ቮግ ከተባለው
መጽሔት የተወሰደው የሚከተለው
አስተያየት የእነሱን ዓይነት
ጭንቀት የሚያሳይ ነው:-
“ድሮ ትሕትና
ጥሩ ሥነ
ምግባር እንደሆነ እንማር
ነበር፤ አሁን ግን
ዝምተኝነት ጉድለት እንዳለብን
ሊያስቆጥረን እንደሚችል እየተማርን
ነው።”
የዚህን ዓለም
መመዘኛ ተከትለው ለመሻሻል
ለሚፈልጉ ሰዎች ይህ
ዓይነቱ ጭንቀት ምናልባት
ተገቢ ሊሆን
ይችላል። ሆኖም አንድ
ክርስቲያን የሚኖረው አቋም
ከዚህ የተለየ
ነው። አንድ
ክርስቲያን አምላክ ትዕቢተኛ
ያልሆኑትን ትሑታን ሰዎች
እንደሚፈልግና በችሎታቸውም እንደሚጠቀም
ያውቃል። ስለዚህ አንድ
ክርስቲያን በራስ ወዳድነት
ዘዴዎች መጠቀም የለበትም።
እርግጥ ነው፣ ከመጠን
በላይ በራሱ
የሚመካ ግለሰብ ተከራክሮ
ወይም አግባብቶ
ጊዜያዊ ክብር ሊያገኝ
ይችል ይሆናል።
ውሎ አድሮ
ግን ይጋለጣል፣
ትሑት መሆንን
ይማራል ወይም ውርደት
ይደርስባታል። ኢየሱስ ክርስቶስ
“ራሱን ከፍ
የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳል፣
ራሱንም የሚያዋርድ ሁሉ
ከፍ ይላል”
ሲል እንደተናገረው
ነው። ማቴዎስ
23:12፤
ምሳሌ 8:13፤
ሉቃስ 9:48
አንድ ደራሲ “የማገኘው ማንኛውም
ሰው በሆነ
መንገድ ይበልጠኛል፤ ምክንያቱም
ከእርሱ የምማረው ነገር
ይኖራል” ሲሉ ጽፈዋል።
የእርሳቸው አነጋገር “ለወገኔ
ይጠቅማል በማለት ወይም
በከንቱ ውዳሴ ምክንያት
አንድ እንኳን
አታድርጉ፣ ነገር ግን
እያንዳንዱ ባልንጀራው ከራሱ
ይልቅ እንዲሻል
በትሕትና ይቁጠር” ከሚለው
ጳውሎስ በመለኮታዊ መንፈስ
አነሣሽነት ለክርስቲያኖች ከጻፈው
ምክር ጋር
ይስማማል። (ፊልጵስዩስ 2:3)
በዚህ ዓይነት
አቅምንና ቦታን ማወቅ
አንድን ሰው ከሌሎች
እንዲማር ያደርገዋል።
ስለዚህ ጠንካራ
ጎንህ ደካማ
ጎንህን የሚያሳይ እንዳይሆን
ተጠንቀቅ። ጉራ ችሎታህንና
ያከናወንካቸውን መልካም ሥራዎች
እንዲያቃልልብህ አትፍቀድ። ባሉህ
ባሕርያት ላይ አቅምንና
ቦታን የማወቅን
ግሩም ባሕርይ
አክልባቸው። አንድ ሰው
በሌሎች ሰዎች ፊት
ከፍ ብሎ
እንዲታይ የሚያደርገው ይህ
ነው። አቅምንና
ቦታን ማወቅ
አንድ ሰው
ከሌሎች ሰዎች ጋር
ጥሩ ግንኙነት
እንዲኖረው ይረዳዋል፤ እንዲሁም
በእግዚአብሄር ዘንድ ተቀባይነት
ያስገኝለታል። ሚክያስ
6:8፤
2 ቆሮንቶስ 10:18
በመጨረሻው ቀን ሰዎች “ትምክህተኞች፣ ትዕቢተኞች፣ ተሳዳቢዎች” ይሆናሉ። እነዚህ ሦስት ባሕርያት አንድ ባይሆኑም ሁሉም ከኩራት ጋር ይዛመዳሉ። የመጀመሪያው ባሕርይ ‘ትምክህተኝነት’ ነው። አንድ መዝገበ ቃላት እንደሚናገረው እዚህ ላይ ትርጉሙ ‘ከሚገባ በላይ ራስን ከፍ ከፍ ማድረግ’ ወይም ‘ማድረግ የማይችለውን አደርጋለሁ ብሎ ተስፋ መስጠት’ ማለት ነው። ስለዚህ አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች እዚህ ላይ “ጉረኞች” የሚለውን ቃል ለምን እንደሚጠቀሙ ሊገባን ይችላል። ቀጥሎ የተጠቀሰው “ትዕቢተኞች” ወይም ቃል በቃል ሲተረጎም “ከሌላው የሚበልጡ መስለው የሚታዩ” የሚለው ነው። በመጨረሻ የተጠቀሰው “ተሳዳቢዎች” ነው። ተሳዳቢዎች ሲባል እግዚአብሄርን
ስለሚያዋርዱ ወይም በእግዚአብሄር
ላይ መጥፎ ቃል ስለሚናገሩ ሰዎች ብቻ መናገሩ ነው ብለው የሚያስቡ ሰዎች ይኖሩ ይሆናል። ይሁን እንጂ ቃሉ በሰዎች ላይ ጎጂ፣ አዋራጅ ወይም የስድብ ቃል የሚናገሩትንም ይጨምራል። ስለዚህ ጳውሎስ የተናገረው አምላክንም ሆነ ሰዎችን ስለሚሳደቡ ሰዎች ነው።
የትዕቢተኛ ስው ባህሪ
በንቀት ላይ የተመሠረተ ኩራት፣ የበላይነት ስሜት፣ እብሪትን ያካትታል፣ ትዕቢት የትሕትና ተቃራኒ ነው። “ትዕቢት” እና “ትዕቢተኛ” ተብለው የተተረጎሙት የግሪክኛና የዕብራይስጥ ቃላት “ትልቅ”፣ “ከፍተኛ” እና “የበላይ” መስሎ መታየት የሚል ትርጉም አላቸው። ትዕቢተኛ የሆነ ሰው ከሌሎች ሰዎች ሁሉ የበላይ ወይም ከፍ ያለ እንደሆነ ይሰማዋል። በመሆኑም እንዲህ ያለው ሰው ብዙውን ጊዜ ከተገቢው በላይ ክብርና ትኩረት እንዲሰጠው ይፈልጋል፤ ሌሎችን በንቀት የሚመለከት ከመሆኑም በላይ አክብሮት በጎደለው መንገድ ይይዛቸዋል።
ትዕቢት ከአስተሳሰብ ጋር ብቻ የተያያዘ መጥፎ ባሕርይ አይደለም። ኢየሱስ ክርስቶስ ትዕቢትን ከግድያ፣ ከሌብነት፣ ከስድብና ከሌሎች ክፉ ድርጊቶች ጋር የፈረጀው ሲሆን እንደነዚህ ያሉት ነገሮች “ከውስጥ ይኸውም ከሰው ልብ” እንደሚወጡ ተናግሯል። (ማር 7:21,
22) የኢየሱስ እናት የሆነችው ማርያም “በልባቸው ሐሳብ ትዕቢተኛ የሆኑትንም በትኗቸዋል” በማለት ስለ ይሖዋ ተናግራለች። (ሉቃስ 1:51) ዳዊትም “ልቤ አይኩራራም” በማለት ወደ ይሖዋ ጸልዮአል። መዝ 131:1፤ ኢሳ 9:9፤ ዳን 5:20
እግዚአብሄርን በትሕትና ሲያገለግል የቆየ ሰው እንኳ ሀብት ወይም ሥልጣን በማግኘቱ አሊያም በቁንጅናው፣ ባገኘው ስኬት፣ በጥበቡ ወይም ከሌሎች በሚያገኘው ሙገሳ ምክንያት ትዕቢተኛ ሊሆን ይችላል። የይሁዳው ንጉሥ ዖዝያ በዚህ ረገድ ምሳሌ ይሆነናል። ለበርካታ ዓመታት ሕዝቡን በጥሩ ሁኔታ ሲያስተዳድር የእግዚአብሄርን በረከት አግኝቶ ነበር። (2ዜና 26:3-5) መጽሐፍ ቅዱስ ከጊዜ በኋላ የሆነውን ሲናገር እንዲህ ይላል፦ “ይሁን እንጂ ዖዝያ በበረታ ጊዜ ለጥፋት እስኪዳረግ ድረስ ልቡ ታበየ፤ በዕጣን መሠዊያው ላይ ዕጣን ለማጠን ወደ እግዚአብሄር ቤተ መቅደስ በመግባት በአምላኩ በእግዚአብሄር ላይ ታማኝነት የጎደለው ድርጊት ፈጸመ።” (2ዜና
26:16) ዖዝያ በትዕቢት ተነሳስቶ አምላክ ለእስራኤል ነገሥታት ፈጽሞ የከለከለውን የክህነት ሥራ ለማከናወን ሞክሯል፤ አምላክ ግን የንግሥናና የክህነት ሥራን ለያይቶ አስቀምጧል።
ጥሩ ንጉሥ የነበረው ሕዝቅያስም በአንድ ወቅት ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን ልቡ ታብዮ ነበር፤ ይህ ባሕርይ ወደሚገዛው ሕዝብም ተጋብቶ እንደነበር ጥርጥር የለውም። ሕዝቅያስ ስኬታማ መሆን የቻለው እግዚአብሄር ስለባረከው ነበር፤ ይሁን እንጂ እግዚአብሄር ላደረገለት ነገር አድናቆት ማሳየትም ሆነ ለዚያ ሁሉ መመስገን ያለበት እግዚአብሄር እንደሆነ መቀበል አቃተው። ፀሐፊው ስለ እርሱ ሲጽፍ እንዲህ ብሏል፦ “ይሁንና ሕዝቅያስ ልቡ ታብዮ ስለነበር ለተደረገለት መልካም ነገር አድናቆት ሳያሳይ ቀረ፤ የእግዚአብሄርም ቁጣ በእሱ፣ በይሁዳና በኢየሩሳሌም ላይ መጣ።” ደስ የሚለው ግን ይህን አደገኛ ዝንባሌ አስወግዷል። ዘገባው በመቀጠል እንዲህ ይላል፦ “ይሁን እንጂ ሕዝቅያስ ስለ ልቡ ትዕቢት ራሱን ዝቅ አደረገ፤ እሱና የኢየሩሳሌም ነዋሪዎች ትሕትና አሳዩ፤ የእግዚአብሄር ቁጣ በሕዝቅያስ ዘመን አልመጣባቸውም።”2ዜና 32:25, 26፤ ከኢሳ 3:16-24 እና ሕዝ 28:2, 5, 17 ጋር አወዳድር።
እግዚአብሄር ትዕቢተኞችን ይቃወማል። ትዕቢተኛ ሰዎች በቅን ሰዎች የሚጠሉ ቢሆንም ከዚህ የሚከፋው እግዚአብሄር አምላክ የሚቃወማቸው መሆኑ ነው። (ያዕ 4:6፤ 1ጴጥ 5:5) ትዕቢት ሞኝነትና ኃጢአት ነው (ምሳሌ 14:3፤ 21:4)፤ እግዚአብሄር ትዕቢተኞችን ይቃወማል እንዲሁም ዝቅ ያደርጋቸዋል። (2ሳሙ 22:28፤ ኢዮብ 10:16፤ 40:11፤ መዝ 18:27፤
31:18, 23፤ ኢሳ 2:11, 17) አንድ ሰው የትዕቢት ባሕርይውን ማስወገድ ካልቻለ ጥፋት ያስከትልበታል። በእግዚአብሄርና በሕዝቦቹ ላይ በትዕቢት የተነሳው የጥንቱ የሞዓብ ብሔር ድምጥማጡ ጠፍቷል። (ኢሳ 16:6፤
25:10, 11፤ ኤር 48:29) አሥሩን ነገድ ያቀፈው የእስራኤል መንግሥት እንኳ በልቡ በታበየና እብሪተኛ በሆነ ጊዜ ከቅጣት አላመለጠም።ኢሳ
9:8-12
አንድ ሰው በልቡ ውስጥ ትዕቢት እንዳይኖር መጠንቀቅ ይኖርበታል። በተለይ የሚያደርጋቸው ነገሮች ሲሳኩለት ወይም ከፍ ያለ ቦታ ወይም ኃላፊነት ሲሰጠው መጠንቀቅ ይኖርበታል። “ኩራት ጥፋትን፣ የትዕቢት መንፈስም ውድቀትን” እንደሚቀድም መዘንጋት አይኖርበትም። (ምሳሌ
16:18) በውስጡ ትዕቢት እንዲያድግ ከፈቀደ ይህ ባሕርይ ሙሉ በሙሉ ሊቆጣጠረውና ከእግዚአብሄር ተቀባይነት ለሌለው አስተሳሰብ አሳልፎ ከሚሰጣቸው ብሎም ሞት ይገባቸዋል ከሚላቸው ሰዎች ተርታ እንዲመደብ ሊያደርገው ይችላል። (ሮሜ 1:28, 30, 32) እንዲህ ያለው ማስጠንቀቂያ በተለይ በእነዚህ “በመጨረሻዎቹ ቀናት” መሰጠቱ በጣም አስፈላጊ ነው፤ ምክንያቱ ለመቋቋም አስቸጋሪ በሆነው በዚህ ዘመን ሰዎች ትዕቢተኞች እንደሚሆኑ አስቀድሞ ተነግሯል።2ጢሞ 3:1,
2
በተጨማሪም የአምላክን ሞገስ ማግኘት የሚፈልግ ሰው ሌሎች የትዕቢት መንፈስ እንዲያድርባቸው ከሚያደርገው ባሕርይ ይኸውም ከሽንገላ መራቅ ይኖርበታል። የምሳሌ መጽሐፍ “ባልንጀራውን የሚሸነግል ሰው፣ ለእግሩ ወጥመድ ይዘረጋበታል” ይላል። (ምሳሌ 29:5)
አንድ ሰው ሌሎችን የሚሸነግል ከሆነ በባልንጀራው ላይ ጥፋት ከማስከተሉም በላይ (“የሚሸነግል አንደበትም ጥፋት ያስከትላል”፣ ምሳሌ 26:28) እሱ ራሱ የአምላክን ሞገስ ያጣል። ሐዋርያው ጳውሎስ ከሽንገላ እና ከትዕቢት ለመራቅ ጥረት አድርጓል።1ተሰ 2:5, 6






0 comments:
Post a Comment