Monday, June 24, 2024

 

ሴቶች

ዘፍ. 2:18 :- “እግዚአብሄር አምላክ እንዲህ አለ:- ‘ሰው ብቻውን መኖሩ መልካም አይደለም። ስለዚህ የጐደለውን የምታሟላና ረዳት የምትሆነውን እፈጥርለታለሁ።’” (እዚህ ላይ እግዚአብሄር ወንዱ ከሴቲቱ የተሻለ ሰው እንደሆነ አልገለጸም። ከዚያ ይልቅ በአምላክ ዝግጅት ውስጥ ሴት የወንድን ባሕርያት የሚያሟሉ ባሕርያት እንደሚኖሯት እግዚአብሄር በቃሉ አመልክቷል። ማሟያ ማለት አንድ ላይ ሲሆኑ አንድ አካል ከሚፈጥሩ ሁለት ነገሮች አንዱ ነው። ሴቶች በቡድን መልክ በአንዳንድ ባሕርያትና ችሎታዎች የላቁ ሲሆኑ፣ ወንዶችም እንዲሁ በሌሎች ነገሮች የላቁ ናቸው። ቆሮንቶስ 11:11, 12 ጋር አወዳድር)

ዘፍ. 3:16:- “[እግዚአብሔርም ለሴቲቱአለ:- . . . ፈቃድሽም ወደ ባልሽ ይሆናል፣ እርሱም ገዥሽ ይሆናል።” (ይህ አዳምና ሔዋን ኃጢአት ከሠሩ በኋላ የተገለጸው ነገር ወንዶች ምን ማድረግ እንዳለባቸው የሚገልጽ ሳይሆን ራስ ወዳድነት ወደፊት የሰው ሕይወት ክፍል መሆኑ ስለማይቀር ወንዶች ወደፊት ምን እንደሚያደርጉ እግዚአብሄር አስቀድሞ ስላወቀ ያንን መናገሩ ነበር። ከዚህ የሰዎች የራስ ወዳድነት አገዛዝ የተነሣ የተስፋፉትን ደስ የማያሰኙ ሁኔታዎች ከዚህ በኋላ በርካታ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ገልጸዋቸዋል። ሆኖም እንዲህ የመሰለውን ጠባይ እግዚአብሄር እንደተቀበለው መጽሐፍ ቅዱስ አይናገርም። ወይም ሌሎች ሊከተሉት የሚገባ ምሳሌ ነው አይልም።)

የራስነትን ቦታ ለወንዶች መስጠት ሴቶችን ዝቅ ያደርጋቸዋልን?

አንድ ሰው በሌላው ራስነት ሥር መሆኑ ዝቅ ተደረገ ማለት አይደለም። የራስነት ቦታ መኖር ነገሮችን ሥርዓት ባለው ዝግጅት ለማከናወን አስተዋጽኦ ያደርጋል። እግዚአብሄር “የሰላም አምላክ ነው እንጂ የሁከት አምላክ አይደለም።” (1 ቆሮ. 14:33) ኢየሱስ ክርስቶስ ከእግዚአብሄር አምላክ ራስነት ሥር ነው። በዚህ ቦታውም ታላቅ እርካታ ያገኛል። ዮሐ. 5:19, 20 8:29 1 ቆሮ. 15:27, 2 አንጻራዊ የሆነ የራስነት ቦታ በተለይ በቤተሰብ ውስጥና በክርስቲያን ጉባኤ ለወንድ ተሰጥቷል። ወንድ በሴት ላይ ፍጹም ሥልጣን እንዲኖረው አልተደረገም፤ ወንድ ስለ ራስነቱ ቦታ አጠቃቀም ራሱ ለሆነው ክርስቶስና ለአምላክ መልስ መስጠት አለበት። (1 ቆሮ. 11:3) በተጨማሪ ወንዶች “እንደ ገዛ ሥጋቸው አድርገው ሚስቶቻቸውን [እንዲወዱ]” እና ለሚስቶቻቸው ‘ክብር እንዲሰጡአቸው’ ታዝዘዋል። (ኤፌ. 5:28 1 ጴጥ. 3:7) እግዚአብሄር ለተጋቡት ሰዎች በሰጠው ዝግጅት ውስጥ በሩካቤ ሥጋ የመርካቱ ችሎታ ለባል ብቻ ሳይሆን ለሚስትም ተሰጥቷል። (1 ቆሮ. 7:3, 4) በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደተገለጸው ባለሞያ የሆነች ሴት የተሰጣት ቦታ በቤተሰቧና በአካባቢዋ ያላትን ዋጋ አጉልቶ ያሳያል። ይህም የባልዋን የራስነት ቦታ ሳትዘነጋ በግሏ ተነሣሥታ ለመሥራት የሚያስችላት ሰፊ መስክ ይሰጣታል። (ምሳሌ 31:10–31) ልጆች አባታቸውን ብቻ ሳይሆን እናታቸውንም ጭምር እንዲያከብሩ መጽሐፍ ቅዱስ ያዝዛቸዋል። (ኤፌ. 6:1–3) መጽሐፍ ቅዱስ መበለቶችን በችግራቸው ለመርዳቱ ጉዳይ ልዩ ትኩረት ይሰጣል። (ያዕ. 1:27) ስለዚህ በእውነተኛ ክርስቲያኖች መካከል ሴቶች ሳይሰጉ ተማምነው ሊኖሩ ይችላሉ፤ በግለሰብ ደረጃ ለራሳቸው እውነተኛ አድናቆትና በሥራቸው ግላዊ እርካታ ሊያገኙ ይችላሉ።

ታማኝ መንፈሳዊ ፍጥረቶቹ የሚገኙበትን የራሱን ድርጅት እንደ አንዲት ሴት፣ እንደ ራሱ ሚስት፣ እንደ ልጆቹ እናት አድርጎ መግለጹ ሴት በእግዚአብሄር ዝግጅት ውስጥ ያላትን ቦታ ያሳያል። (ራእይ 12:1 ገላ. 4:26) እንዲሁም በመንፈስ የተቀባችው የኢየሱስ ክርስቶስ ጉባኤ የእርሱ ሙሽራ እንደሆነች ተነግሮናል። (ራእይ 19:7 21:2, 9) በመንፈሳዊ አመለካከት በወንድና በሴት መካከል ምንም ልዩነት የለም። ከክርስቶስ ጋር ሰማያዊ መንግሥት እንዲካፈሉ ከተጠሩት መካከል ወንዶችም ሴቶችም ይገኛሉ። ገላ. 3:26–28

ክርስቲያን ሴቶች በአንዳንድ ወቅቶች ራሳቸውን የሚሸፍኑት ለምንድን ነው?

ቆሮ. 11:3–10:- “የወንድ ሁሉ ራስ ክርስቶስ፣ የሴትም ራስ ወንድ፣ የክርስቶስም ራስ እግዚአብሔር [ነው።] . . . ራስዋን ሳትሸፍን የምትጸልይ ወይም ትንቢት የምትናገር ሴት ሁሉ ራስዋን [ባልዋንታዋርዳለች፤ . . . ወንድ የእግዚአብሔር ምሳሌና ክብር ስለሆነ ራሱን መከናነብ አይገባውም፤ ሴት ግን የወንድ ክብር ናት። ሴት ከወንድ ናት እንጂ ወንድ ከሴት አይደለምና። ሴት ስለ ወንድ ተፈጠረች እንጂ ወንድ ስለ ሴት አልተፈጠረምና። ስለዚህ ሴት ከመላእክት የተነሣ በራስዋ ሥልጣን ሊኖራት ይገባል።” (አንዲት ክርስቲያን ሴት ተገቢ በሆኑ ወቅቶች ራሷን መሸፈኗ በአምላክ ለተቋቋመው የራስነት ዝግጅት ክብር እንደምትሰጥ አንድ ማስረጃ ነው። ክርስቶስ ቲኦክራሲያዊ የራስነት ሥልጣንን ያከብራል፤ ወንድና ሴት እንደዚሁ እንዲያደርጉ ግዴታ አለባቸው። የመጀመሪያው ሰው አዳም ከሴት የተወለደ ሳይሆን በአምላክ የተፈጠረ ነበር። እግዚአብሄር ሔዋንን ሲፈጥር ከአዳም አንድ የጎን አጥንት ወስዶ እንደመሠረት ተጠቅሞበታል፣ እግዚአብሄርም ሴቲቱ ለአዳም ረዳቱ እንደምትሆን ገልጿል። ስለዚህ መጀመሪያ ለተፈጠረው ሰው የራስነት ቦታ ተሰጥቶታል። ወንድ ‘በሚጸልይበት ወይም ትንቢት በሚናገርበት’ ጊዜ ራሱን አይሸፍንም ምክንያቱም ራስነትን በተመለከተ ወንድ ‘የአምላክ ምሳሌ’ ነው፤ ማለትም የራሱን ቤተሰብ በተመለከቱ ጉዳዮች ሌላ ምድራዊ ራስ የለውም። ይሁን እንጂ ሴት ራሷን ሳትሸፍን ‘መጸለይ ወይም ትንቢት መናገር’ አምላክ ለወንድ ለሰጠው ቦታ ክብር አለመስጠት እንደሆነ ያሳያል፣ እርሱንም ያሳፍረዋል።

አንዲት ሴት ራሷን መሸፈን የሚያስፈልጋት መቼ ነው?

አንዲት ሴት ራሷን መሸፈን ያለባት ቆሮንቶስ 11:5 ላይ እንደተገለጸው ‘በምትጸልይበትና ትንቢት በምትናገርበት ጊዜ’ ነው። በግልዋ ስትጸልይ ወይም ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ትንቢቶች ከሌሎች ጋር ስትወያይ ራሷን መሸፈን ያስፈልጋታል ማለት አይደለም። ይሁን እንጂ ባልዋ የሚያከናውናቸውን ወይም ሌላ ወንድ የሚያደርጋቸውን አምልኮ ነክ ጉዳዮች ስታከናውን የወንድን የራስነት ቦታ እንደምታከብር በውጪ ምልክት እንዲሆን ራሷን መሸፈን አለባት። ራሷና ሌሎችን በመወከል የምትጸልይ ከሆነ ወይም መደበኛ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ስትመራ፣ ባልዋ በሚገኝበት ስታስተምር ባልዋ የእርሷ ዓይነት እምነት ባይኖረውም እንኳ ራሷን መሸፈን አለባት። ነገር ግን ልጆችዋን የማስተማር መለኮታዊ ሥልጣን ስለተሰጣት ባልዋ በማይኖርበት ጊዜ ራሳቸውን ካልወሰኑ ትናንሽ ልጆች ጋር ስትጸልይ ወይም ስታስጠና ራሷን መከናነብ አያስፈልጋትም። ከዚህ ለየት ባለ ሁኔታ ራሱን የወሰነ የጉባኤ አባል የሆነ ወንድ በተገኘበት ወይም ጐብኚ ተጓዥ የበላይ ተመልካች አብሯት በሚያገለግልበት ጊዜ አስቀድሞ ቀጠሮ የተያዘለት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ስትመራ ራሷን መከናነብ አለባት፤ ጸሎት ግን እርሱ ማቅረብ አለበት።

ሴቶች ኮስሜቲክስ ቢጠቀሙ ወይም ጌጣጌጥ ቢያደርጉ ተገቢ ነውን?

ጴጥ. 3:3, 4:- “ለእናንተም ጠጉርን በመሸረብና ወርቅን በማንጠልጠል ወይም ልብስን በመጐናጸፍ በውጭ የሆነ ሽልማት አይሁንላችሁ፣ ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ የዋህና ዝግተኛ መንፈስ ያለውን የማይጠፋውን ልብስ ለብሶ የተሰወረ የልብ ሰው ይሁንላችሁ።” (ይህ ማለት ሴቶች ጌጣጌጥ ማድረግ የለባቸውም ማለት ነውንበፍጹም አይደለም፤ ሴቶች ልብስ መልበስ የለባቸውም ማለት እንዳልሆነ ሁሉ ይህም እንደዚያ ማለት ነው። ሆኖም ግን እዚህ ላይ የፀጉር አበጣጠራቸውንና የልብስ አለባበሳቸውን በተመለከተ ሚዛናዊ የሆነ አመለካከት ይዘው በቅድሚያ ለመንፈሳዊ ጌጥ ትኩረት እንዲሰጡ ተመክረዋል)

ጢሞ. 2:9, 10:- “ሴቶች በሚገባ ልብስ ከልከኝነትና ከጤናማ አስተሳሰብ ጋር ራሳቸውን እንዲሸልሙ እወዳለሁ፤ ነገር ግን በፀጉር አሠራር ዘዴና በወርቅ ወይም በእንቁ ወይም በዋጋው እጅግ በከበረ ልብስ ሳይሆን እግዚአብሔርን እናከብራለን ለሚሉ ሴቶች በሚስማማ መንገድ ይኸውም በመልካም ሥራዎች ይሁን።” (በአምላክ ዘንድ በእርግጥ ዋጋ ያለው ምንድን ነውየአንድ ሰው የውጪ ገጽታ ወይስ የአንድ ሰው ልብ ሁኔታአንዲት ሴት የፆታ ብልግና እየፈጸመች ብትኖር ግን ኮስሜቲክስ ባትጠቀምና ጌጣ ጌጥ ባታደርግ አምላክ ደስ ይሰኛልንወይስ ቅባትና ጌጣ ጌጥ በልክ የሚያደርጉትንና ጤናማ አስተሳሰብ ያላቸውን፣ በቅድሚያ ራሳቸውን በአምላካዊ ጠባዮችና ክርስቲያናዊ ጠባይ የሚሸልሙትን ሴቶች ይቀበላልየእግዚአብሄር ቃል  እንዲህ ይላል:- “ሰው እንዲያይ እግዚአብሔር አያይምና። . . . ሰው ፊትን ያያል፣ እግዚአብሔር ግን ልብን ያያል።” 1 ሳሙ. 16:7)

ምሳሌ 31:30:- “ውበት ሐሰት ነው፣ ደም ግባትም ከንቱ ነው፤ እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች።

ሴቶች የጉባኤ አገልጋዮች መሆን ይገባቸዋልን?

የጉባኤ የበላይ ተመልካችነት ኃላፊነት የተሰጣቸው ወንዶች መሆናቸው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተገልጿል። የኢየሱስ ክርስቶስ 12 ሐዋርያት ሁሉም ወንዶች ነበሩ፣ በኋላም የክርስቲያን ጉባኤዎች የበላይ ተመልካቾችና አገልጋዮች ነበሩ። (ማቴ. 10:1–4 1 ጢሞ. 3:2, 12) ሴቶች በጉባኤ ስብሰባዎች “በሁሉ ነገር እየተገዙ በጸጥታ እንዲማሩ” ተመክረዋል፣ በጉባኤ ወንዶችን የሚፈታተኑ ጥያቄዎች አያነሡም። ሴቶች የሚናገሩት ነገር ታዛዥነት እንደጎደላቸው የሚያሳይ ከሆነ እንዲህ በመሰሉ ስብሰባዎች ላይ ‘አይናገሩም (1 ጢሞ. 2:11, 12 1 ቆሮ. 14:33, 34) ስለዚህ ሴቶች ምንም እንኳ በጉባኤ ሥራዎች ጠቃሚ አሰተዋጽኦ ቢያበረክቱም ብቁ ወንዶች እያሉ ጉባኤውን እንዲመሩ ወይም ጉባኤውን በማስተማር ቀዳሚ እንዲሆኑ አልተደረገም። ሆኖም ሴቶች ከጉባኤ ስብሰባዎች ውጪ ሰባኪዎች፣ አዋጅ ነጋሪዎች፣ የምሥራቹ አገልጋዮች መሆን ይችላሉን?  በጰንጠቆስጤ ዕለት መንፈስ ቅዱስ በወንዶችና በሴቶች ላይ ፈሰሰ። ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ኢዩኤል 2:28, 29 ጠቅሶ ሲገልጽ እንዲህ አለ:- “በመጨረሻው ቀን እንዲህ ይሆናል፤ ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፣ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ፣ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ፤ ደግሞም በዚያች ወራት በወንዶችና በሴቶች ባሪያዎቼ ላይ ከመንፈሴ አፈስሳለሁ ትንቢትም ይናገራሉ።” (የሐዋሥራ 2:17, 18) ዛሬም በተመሳሳይ ሴቶች ከቤት ወደ ቤት በመሄድ እየሰበኩና የቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች እየመሩ በክርስቲያን አገልግሎት በሚገባ ይካፈላሉ። በተጨማሪ መዝሙር 68:11 ፊልጵስዩስ 4:2, 3 ተመልከት።

የሮሜ መልዕክት ሐተታዊ መግለጫ በዶ/ አመለወርቅ ከተጻፈው የተወስደ

በሮሜ 16:1-16

በይፋ  በዚህ ክፍል ከተስጠው ስላምታ እንደተገኘው “ዲያቆን“ የሚለው ቃል ትርጉሙ “አገልጋይ“ ማለት እንደሆነ

ነው። የዲያቆን ደረጃው 1 ጢሞ. 38-13 ተጠቅሷል። “ዲያቆን“ የሚለው ቃል የሚገኘው በሮሜ 16ላይ ሲሆን ትርጉሙ “አገልጋይ“ ስሙም የተያያዘው ከሴት ስም ጋር በመሆኑ በሐዋሪያት ዘመን የሴት ዲያቆናት እንደነበሩ ያመለከታል። በሮሜ ምዕራፍ 166 12 እንደዚሁ የሴቶች ዲያቆናት እንደነበሩ ያመለክታል። ለአስተዳደር ሥርዓት ማለትም ለዚሁ አገልግሎት የተመረጡ የሴቶችን

አመል በተመለከተ 1 ጢሞ. 311 ቲቶ 2ተመልክቷል።

በሮሜ 161-2 ያሉት ጥቅሶች ፌበን በክራክራኦስ ከተማ በምሥራቁ ቆሮንጦስ የባህር በር 9 ማይልስ ያህል ከዋናው ከተማ በምትርቀው ቤተክርስቲያን ዲያቆን እንደሆነች ያመለክታሉ። በቅዱሳን ዘንድ ስለ እርሷ የሚታወቀው ፌበን እራሷን ለጌታ አሳልፋ የስጠች የክርስቲያን ሴት እንደሆነች ነው። ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ ለሚኖሩ ቅዱሳን የጻፈላቸውን የሮሜን መልዕክቱን ወደ ሮማ ለሌላም ጉዳይ ወይም ሥራ ስትሄድ አብራ የሮሜን መልዕክቱን በሮማ ለሚገኙ ክርስቲያኖች ያደርስቸው ፌበን ነች። ቅዱስ ጳውሎስ በሮማ ላሉት ቅዱሳን እውነተኛ እራሷን አሳልፋ የስጠች የክርስቶስ አገልጋይ እንደሆነችና ከእርሱም ጋር በአገልግሎት የተጠመደች ስለሆነች የሮማ ቅዱሳን እንዲተባበሯት እንደጠየቀ ያመለክታል።

ወንድና ሴት በእግዚአብሔር ፊት ያላቸው እኩልነት ለጳውሎስ ግልጽ ነው። ቢሆንም ግን በቤተክርስቲያንና በኅብረተሰብ መካከላ ያላቸው የጥሪና የአገልግሎት ልዩነት በዚህ የእኩልነት አቋም ይወገዳል ማለት አይደለም።  ቅዱስ

ጳውሎስ የሴት ጠላት እንደነበር ወይም ደግሞ ሴትን የሚያዋርድ (የሚንቅእንደነበር ማረጋገጫ ይገኛልንእሱ ራሱ ከትዳር ይልቅ ሳያገባ መኖርን መምረጡ ከክርስትና ሕይወት ጋር የሚሄድ ነውለቆሮንቶስ ሰዎች ልክ የእሱን ዓይነት ሕይወት እንዲይዙ ማለትም ሳያገቡ እንዲኖሩ መምከሩ፤ በቆሮንጦስ የነበረውን ልቅ ዓይነት ሕይወትን ተመልክቶ ያስተላለፈው በመሆኑ የሚያስደንቅ ምክር አይደለም። የቆሮንጦስ ሰዎች በሜዲትራንያን አካባቢ ቅጥ በሌለው በምንዝርና ሕይወታቸው የታወቁ ነበሩ። ቢሆንም ግን “… ለእያንዳንዱ እግዚአብሔር የተለየ ስጦታ ሰጥቶታል፤ አንዱ አንድ ዓይነት ስጦታ፤ ሌላውም ሌላ ዐይነት ስጦታ አለው” (1ቆሮ.77)

ብዙ የቅዱስ ጳውሎስን ጽሑፍ የሚያነቡ፣ አንብበውም የሚመራመሩ፣ ዛሬም ያሉ በፊትም የነበሩ፤ ቅዱስ ጳውሎስ ስለ ሴት የነበረውን አስተሳሰብ ግልጽ ሊያደርጉ ይፈልጋሉ። ሆኖም ግን በመጨረሻ ላይ የሚሰጡት ድምዳሜ እንደብዛታቸው የተለያየ ነው። በተለይ ደግሞ ክርስቲያን ሴት  ልጅ ቅዱስ ጳውሎስ የሚለውን አንዱን ክፍል ብቻ ይዛ፤ ጥያቄ ልትጠይቅ፣ እውነተኛ ትርጉሙ ምን እንደሆነ ለማወቅ እንደምትጠይቅ ጥርጥር የለውም።

ቅዱስ ጳውሎስ የጠርሴስ ልጅ እንደመሆኑ መጠን፤ በጥንታዊት ቤተክርስቲያን ልዩ ቦታ የነበረውና ልዩ አዎንታዊ ተጽዕኖ ያሳደረ ሰው ነው። የእርሱ መልእክቶች ወንጌል ከመጻፉ በፊት የተጻፉና የተሰራጩ በመሆናቸው በመጀመርያዎቹ ክርስቲያኖቹ ሕይወት ላይ የተወው ጫና በጣም ግልጽ ነው። ስለ  ቅዱስ ጳውሎስ የሕይወት ታሪክና ማንነትና ሐሳቦች ምንጮቻችን የሐዋርያት ሥራና የራሱ መልእክቶች ናቸው።

አስተዳደጉና የተኮተኮተበትን ሁኔታም ከተመለከትን እሱ በጣም ሕግ አጥባቂዎች ከሆኑት ከአይሁድ ወገን ሲሆን (የሐዋ.223 ፊልጵ. 35-6)  በደማስቆ መንገድ ላይ የተፈጸመው ፍጻሜ፣ ጳውሎስ ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ መመለሱና መለወጡ፣ የነበረውን አስተሳሰብ፣ አኗኗርና አመለካከት ገለባበጠበት። በፊት ከነበረው አስተሳስብ የተለየ መንገድ እንደሚይዝ አደረገው። ከአረማዊነት ሆነ ከአይሁድነት ወደ ክርስትና የመጡትን ማኅበራተ-ክርስትና በመሠረተበትም ጊዜም ቢሆን ግላዊ አስተሳሰቡን፣ ካገኛቸው ኅብረተሰብ አኗኗር፣ በግልጽ ከክርስትና ሕይወትና ከወንጌል ትምህርት፤ በኢየሱስ ክርስቶስ ከመጣው ትምህርት ጋር የማይቃረነውን ሁሉ ተጠቀመበት። ሴቶችን በሚመለከት የነበረው አስተሳሰብ ደግሞ ከአባባሉና አጻጻፉ የምንገነዘበው ነው። ብቁዎችና ጎበዝ የስብከተ ወንጌል ተባባሪ የሆኑ ሴቶች እንደነበሩት ጳውሎስ ራሱ የሚገልጸው ነው። ፌቨንን ብቻ መጥቀስ ይበቃል። በቅንክርኤ ቤተክርስቲያን ዲያቆን የነበረች ናት (ሮሜ.161) ፌቨን ብቻ ሳትሆን በእምነት ብሩህ ኮከቦች የነበሩትን የጢሞቴዎስ እናትንና አያትን፤ ሌሎችም ቤተክርስቲያንን እምነት በማነጽ እንደ ምሳሌ የጠቅሳቸዋል። በገላትያ መልእክት ውስጥ በእምነቷ ሣራ ብቻ ሳይሆን፤ ማርያምንም አዳኙን በሥጋ በመውለዷ ይጠቅሳታል (ገላ.45 421)

በኦሪት ዘፍጥረት የመጀመርያዎቹ ሁለት ምዕራፎች ስለ ሰው አፈጣጠር የሚናገሩ አሉ። “እግዚአብሄር ሰውን ፈጠረ፤ . . . ወንድና ሴትም አድርጎ ፈጠራቸው” (127) “እግዚአብሔር አምላክ አፈር ከመሬት ወስዶ ሰውን ፈጠረው፤ . .. “ከአዳም ከወሰዳት አጥንት ደግሞ ሴትን ፈጠረ” (27.22) ” በምዕራፍ ሦስት አዳምና ሔዋን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ እንዳፈረሱ ይናገራል። “ሔዋን ደግሞ . .  ከዛፉ ፍሬ ወስዳ በላች፤ ለአዳምም ሰጠችው፤ እሱም በላ (36)  ስለዚህ 54- 56 አካባቢ ቅዱስ ጳውሎስ የጻፈው የመጀመርያው ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች “ባል የሚስት ራስ ነው” ሲል ሳለ፤ ለዚህ ደግሞ እንደ መከላከያ አድርጎ “ሴት ከወንድ እንጂ ወንድ ከሴት አልተገኘም” ሲል (1ቆሮ.113,8) በኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 22 ያለውን በማሰብ እንደሆነ የሚያከራክር አይደለም። ከሱም ጋር ጥንታዊ ልማድና የአይሁድ አስተሳሰብ፤ ለሴቶች ምንም ግምት የማይሰጥ በቅዱስ ጳውሎስ ጭንቅላት ውስጥ እንዳለ መዘንጋት የለብንም።  በዚህ ሁሉ አስተሳሰብ ብሎም ልማድና ሁኔታ ያደገ ጳውሎስ፤ እዚህ ላይ የሰጠው ድምዳሜው ላይ በመድረሱ፤ ማለት ብዙ ሰዎች በተሰበሰቡበት መንፈሳዊ ጉባኤ ሴቶች እንዲናገሩ አለመፍቀዱ የሚያስገርም አይደለም። በጊዜው ልማድ ለመናገር የሚያበቃ እውቀትና ትምህርት እንዳልነበራቸው ግልጽ ነው። (1ቆሮ.113-13 1434-35) ተመሳሳይ ሐሳቦች በሌሎቹ ጽሑፎቹ የማይገኝ አይደለም (ኤፌ.522-23 1ጢሞ.29-15)

ከአረማዊነት ወደ ክርስትና የገቡ የገላትያ ሰዎች በጻፈው መልእክት፤ የጳውሎስ ትምህርተ-መለኮታዊ ትኩረቱን የሚገልጹ ብሩሕ ቃላቶች እናገኛለን። “ሁላችሁም በኢየሱስ ክርስቶስ አንድ ስለሆናችሁ በአይሁዳዊና በግሪካዊ፣ በአገልጋይና በጌታ፣ በወንድና በሴት መካከል ምንም ልዩነት የለም” (ገላ.328) “ወንድ ሴት” የሚለው አባባል በኦሪት ዘፍጥረት 127 ያለውን እንደሚያመለክት ጥርጥር የለውም። በተለይ በግሪካዊ አባባሉ ድሮ በሰባ ሊቃውንት (ሴፕትዋጂንትያለውን የሚያንጸባርቅ ነው።

በጊዜያችን ቤተክርስቲያን በጉባኤዎች  የምታስተምረው ትምህርት፤ በተለይ ስለ ግልጸት ወይም የእግዚአብሄር ቃል በሚናገረው ቁጥር 12 ላይ የሚሠጠው መሠረታዊ ነጥብ አለ “እግዚአብሔር መጽሐፍ ቅዱስን በሰዎች አድርጎ ስለሚናገረን፤ የመጽሐፍ ቅዱስን ትርጓሜ የሚተነትን ሰው፣ ልክ  እግዚአብሄር ሊገልጽልን በፈለገው ዓይነት እንዲገባው ከፈለገ፤ ጸሐፊዎቹ ሊሉትና ሊረዱት የፈለጉትን ትርጓሜ፤ እንዲሁም እግዚአብሄር በቃላቶቻቸው አድርጎ ሊገልጸው የፈለገውን ሁሉ ለማወቅ በጥንቃቄ መመርመር ያስፈልገዋል።” የእግዚአብሄር  ቃል የጊዜውን አነጋገርና አቀራረብ ወስዶ ነው ወደኛ የሚመጣው። እኛ ግን ከጊዜ ጋር የሚለዋወጠውንና የማይለዋወጠን ለይተን ለማየት እንጥራለን። ሥነ ሥርዓትን በሚመለከትና እምነትንና ድኅነትን በሚመለከት ለይተን መመልከት ይኖርብናል። ስለ ሴቶች የሚሰጠው መመርያ ደግሞ የሥነ ሥርዓት ጉዳይ ልማድ እንጂ እንደ ትምህተ መለኮት፤ ወይም ደግሞ ያለ እኩልነት ምልክት ሆኖ መወሰድ የለበትም።

ይህ ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክቱ ስለ ሴቶች የተናገረውን ግልጽ ሊያደርግልን ይችላል። ስለዚህ ጳውሎስ የሚለውን ሁሉ ከጊዜው ሁኔታ ጋር አዛምደን ካነበብነው፤ ጳውሎስ የሴቶች ተቃዋሚ ሳይሆን ደጋፊ እንደሆነ ነው። ባለፉት ዘመናት ቅዱስ ጳውሎስን በሚመለከት ብዙ ጽሑፎችን ያበረከቱ ስለ ሴቶች ያለውን አቋም ሲያንጸባርቁ የነበራቸው የግንዛቤ ችግር ቃላቱን ከነባራዊው ሁኔታ ነጥለው መውሰዳቸው ነው። ከአባባሉ በስተጀርባ ያለውን፤ ወይም በመሥመሮች መካከል የተጻፈውን ሃሳብ ቆፍረን ማግኘቱ ትክክለኛውን ሁኔታ መገንዘብ ያስችለናል።

ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ ምዕራፍ የፌበን አገልግሎቷን እውቅና በመልዕክቱ ውስጥ አንስቷል ይህም የሚያመለክተው በዚያን ዘመን የተነሱትን የሴቶች አገግላዮች ከአይሁድ ባህልና ሥር ዓት አልፎ ለሴቶች አገልግሎት የስጠውን እውቅናና የሴቶች ደጋፊ እንጂ ተቃዋሚ ያለመሆኑን ያመለክታል።

በሮሜ 161-2 በተመለከቱት ጥቅሶች ውስጥ ፌበን በክንክራኦስ ባለች ቤተክርስቲያን “ዲያቆኒት“ በግሪኩ ቃል (ዳያኮኖን)  እንደሆነች ያመለክታሉ። ፌበን  በሮሜ 1-2 በተጻፉት ጥቅሶች መስረት በክንክራኦስ ባለችው ቤተክርስቲያን ዲያቆኒት ነች። “አገልጋይ“ በግሪክ (ዳይኮኖንቃሉ ዲያቆን ሲሆን የሚያመለክተው የሴቶ ዲያቆኖችን የአግልግሎት ቢሮ ነው። እንደነዚህ አይነት ሴቶች መታየት ያላባቸው እንደዲያቆኖች ሚስቶች 1 ጢሞ. 311 እንደተመለከተው ወይም ባላቸው የሞተባቸው የእምነት ሴቶች በቤተክርስቲያን የሚረዱትን 1 ጢሞ. 59 10 እንደተመለከተው ያሉት ናቸው። በዚህ ክፍል ስለ ፌበን አገልግሎት የበለጠ የሚገልጻት “እረዳት“ አገልጋይ የተባለች እንደሆነ ነው የሚሉ የሥነ-መለኮት ምሁራን አሉ።

የሮሜ የመልዕክቱ ጸሐፊ የጀመረው በሴት የሆነበት ምክንያት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በብሉይም ሆነ በሐዲስ አያሌ ሴቶች በአገልግሎት የነበራቸው ድርሻ ስፊ ስለነበረና በሐዲስ ኪዳንም ጊዜ ሴቶች በቤተክርስቲያን አገልግሎት ከባዱን ሽክም የሚሽከሙት እነርሱ ስለሆኑ ነው። በብሉይም ሆነ በሐዲስ ኪዳን የእምነት ሴቶች የእግዚአብሄርን አገልግሎት ለማራመድ እንደመሳሪያ ሆነው በመደገፍ ያገለገሉትን እግዚአብሄርም ታሪክም አይረሳቸውም ብዬ አምናለሁ።

ሮሜ 163-16

ጵሪስቂላና አቂላ በአገልግሎት ቅዱስ ጳውሎስ ጋር የተጠመዱ ነበሩ። ቅዱስ ጳውሎስ በእርሱ ዘንድ በጣም ውድ የሆኑት ባልና ሚስት የቅዱሳን ስም በመጥቀስ ለጵሪስቂላና ለአቂላ በዚህ ክፍል ስላምታ እንዲቀርቡለት ይጠይቃል። እነዚህን ቅዱሳን ያገኛቸው በቆሮንጦስ በሁለትኛው የወንጌል አገልግሎት ጉዞው ሲሆን እነዚህም ቅዱሳን የእግዚአብሄርን አገልግሎት በተመለከተ ጠንካራ ስራተኞች እንደሆኑ ቅዱስ ጳውሎስ ይመስክራል።

ሮሜ 16እና 4 በተመለከቱት ጥቅሶች እንደተገለጸው ቅዱስ ጳውሎስ ከጵሪስቂላ ከባለቤቷ ከአቂላ ጋር አብረው እንዳገለገሉ ያመለክታል።  በሐዋሪያት ሥራ ምዕራፍ 181-3 226 1 ቆሮ. 1619 2 ጢሞ. 419 እንደተጠቀስው ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር በአገልግሎት ለሕይወታቸው አስጊ በሆኑ ሁኔታዎች በማለፍ ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር እንዳገለገሉ ያመለክታል። በሐዋሪያት ሥራ ውስጥ እንደተጠቀስው ጵሪስቂላን አቂላ ድንኳን ሰፊዎች ነበሩ የቅዱስ ጳውሎስም ሥራ ድንኳን መስራት በመሆኑ በቆሮንጦስ በነበሩበት ጊዜ በሐዋሪያት ሥራ 181-3 እንደተጻፈ አብረው ስረተዋል። ጵሪስቂላና አቂላ በዔፌሶንና በቆሮንጦስ በሌሎችም ሥፍራዎች ሕይወታቸው በአደጋ ላይ በሆነበትም ጊዜ አብረውት ነበሩ። ጵሪስቂላና አቂላ ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር የተጠመዱት በድንኳን ሥራ ሙያቸው ብቻ ሳይሆን በወንጌልም አገልግሎት በተለይም በአሕዛብ ወይም በአረማውያን አባያተክርስቲያናት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ተሳትፎ አድርገዋል።

በመጀመሪያው መቶ ዘመን በነበረው የክርስቲያን ጉባኤ ውስጥ የሴቶች ሚና ምን ነበርሴቶች አገልጋዮች መሆን ይችላሉኢየሱስ ተከታዮቹ ምሥራቹን እንዲሰብኩና ደቀ መዛሙርት እንዲያደርጉ መመሪያ ሰጥቷቸዋል። (ማቴ. 28:19, 20 ሥራ 1:8) የምሥራቹ አገልጋዮች እንዲሆኑ የተሰጠው ይህ ተልእኮ ሁሉንም ክርስቲያኖች ይኸውም በየትኛውም የዕድሜ ክልል ያሉ ወንዶችንና ሴቶችን የሚመለከት ነው። ሐዋርያው ጴጥሮስ 33 .በዋለው የጴንጤቆስጤ ዕለት ፍጻሜውን እንዳገኘ የተናገረው በኢዩኤል 2:28, 29 ላይ የሚገኘው ትንቢት ይህን ያሳያል። ጴጥሮስ እንዲህ ብሏል፦ “እግዚአብሄር  እንዲህ ይላል:- ‘በመጨረሻው ቀን መንፈሴን በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ አፈሳለሁ፤ ወንዶች ልጆቻችሁና ሴቶች ልጆቻችሁ ትንቢት ይናገራሉ፤ . . . በዚያ ቀን በወንዶች ባሪያዎቼና በሴቶች ባሪያዎቼ ላይ ሳይቀር መንፈሴን አፈሳለሁ፤ እነሱም ትንቢት ይናገራሉ።’” (የሐዋሥራ 2:17, 18) ቀደም ሲል እንዳየነው ወንጌላዊው ፊልጶስ ትንቢት የሚናገሩ አራት ሴቶች ልጆች ነበሩት።የሐዋሥራ 21:8, 9

በጉባኤ ውስጥ ከማስተማር ጋር በተያያዘ ግን ክርስቲያን የበላይ ተመልካቾችና የጉባኤ አገልጋዮች ሆነው መሾም ያለባቸው ወንዶች ብቻ እንደሆኑ የእግዚአብሄር  ቃል ይናገራል። (1 ጢሞ. 3:1-13 ቲቶ 1:5-9) ደግሞም ጳውሎስ “ሴት ዝም እንድትል እንጂ እንድታስተምር ወይም በወንድ ላይ ሥልጣን እንዲኖራት አልፈቅድም” በማለት ተናግሯል።ጢሞ. 2:12

ጥቅስ 5  በዚህ ጥቅስ ጵሪስቂላና አቂላ በቤታቸው ቅዱሳንን ይስበስቡ እንደነበረና ቅዱሳኑ በምንም አይነት ሁኔታዎች ለክርስቶስ የሚቆሙ እንደሆኑም ያመለክታል። ቅዱስ ጳውሎስ ከላይ እንደተጠቀስው የጠበቀ የአገልግሎትም ሆነ የሙያ ግንኙነት ስለነበራቸው ለእነዚህም ቅዱሳን ስላምታ እንዲያቀርቡለት የጠየቀው ከዚህ የተነሳ ነው። ጵሪስቂላና አቂላ ከአሕዛብ ወይም ከአርማውያን ወደ ክርስትና ለመጡት የአጥቢያ አብያተክርስቲያናት የቤት ለቤት አገልግሎትን በተመለከተ ትልቅ ድርሻ እንዳላቸው 1 ቆሮ. 16 19 ቆላ. 415 ፊልሞና 2 ያመለክታሉ። በቅዱስ ጳውሎስ ጊዜ የነበሩት አብያተክርስቲያናት የቤተክርስቲያን ሕንጻዎች የሏቸውም ስለሆነም የሮማ ግዛት መአከል በሆነው በሮማም ቅዱሳን የሚስበስቡት በቤት ውስጥ ነበር።

ቅዱስ ጳውሎስ ከእርሱ ጋር ያገለገሉትን አጋልጋይዮች ሌሎችንም የሕይወት ምስክርነታቸውንና በወንጌል አገልግሎት ያደረጉትን አስተዋጽኦ  ከስላምታ ጋር አብሮ በሮሜ 165-16 ባሉት ጥቅሶች ያነሳቸዋል እነዚህም ቅዱሳን የሚከተሉት ናቸው።

·         ለአንጤኔጦን - ከስሳያ ለክርስቶስ በኩራት ለሆነው

·        ለማርያስለናነተ ብዙ ለደከመች

·        ለላንዲራኒቆንና ልዩልያንክርስቶስን በማመን ለቀደሙኝ አብረውኝም ለታስሩ ዘመዶቼ

·        ለጵልያጦንበጌታ ለምወደው

·        ለኢሩባኖን - በክርስቶስ አብሮን ለሚስራ

·        ለስንጣከን - ስላምታ አቅርቡልኝ

·        ለዔጤሌን-በክርስቶስ በመሆኑ ተፈትኖ ለተመስገነው

·        ከአርስጣባሉ ቤት - ላሉት ስዎች

·        ለልሄሮድዩና ለዘመዴ

·        ከንርቀሱ ቤት ስዎችበጌታ ላሉት

·        ለፕሮፌሞናና ለጢሮፈምሳ - በጌታ ሆነው ለሚደክሙት

·        ለጠርሲዳ - በጌታ እጅግ ለደከመች ለተወደደች

·        ለሩፎን - በጌታ ሆኖ ለታወቀ ለእኔና ለእርሱም እናት

·        ለአፋላንሶንጳ ለሔሮሜንም ለጳጥሮባም ለሔርማንም ከእነርሱ ጋር ላሉት ወንድሞችም

·        ለፍላጎንና ዩልያ ለኔርያና ለእህቷም ለአልጦንም ከእርሱ ጋር ላሉት ቅዱሳን ሁሉ

የክርስቶስ አብያተክርስቲያናት ሁሉ ስላምታ ያቀርቡላችኋል።

ቅዱስ ጳውሎስ በርሜ 1614-16 ባሉት ጥቅሶች የተጠቀሱት ቅዱሳን የቄሳር አገልጋዮች የነበሩ ናቸው።  ወንጌል በሮማ ግዛት ዝነኛ በሆነው በቄሳር ቤተመንግሥት ውስጥ ገብቶ የስዎችን ነፍስ እንዳዳነ እናያለን። እነዚህ ስዎች ቅዱስ ጳውሎስ ጌታ በሕይወታቸው አስደናቂ ነገር ስላደረገ በስም ለይቶ እንደሚያውቃቸው  5- 16 ያሉት ጥቅሶች ያመለክታሉ። ከነዚህ ስዎች  መሃከል ብዙዎቹ ወደ ክርስትና የመጡት እርሱ በስጠው የወንጌል አገልግሎት እንደሆነም በጥቅስ 5 ላይ ተጽፎአል። እነዚህ ቅዱሳን  በቅዱስ ጳውሎስ የወንጌል አገልግሎት ውስጥ በተለያየ መልኩ ያደርጉትን አስተዋጽኦ ያስታውሳል። ከዚህ በላይ 163-16 ባሉት ጥቅሶች ውስጥ የተጠቀሱት ስሞች በሮማ በሚገኘው ጥንታዊ የስማዕታት የመቃብር ቦታ በወንጌል አገልግሎት ሰለተስው ከስማዕታቱ መሃከል ስማቸው ተጽፎ ይገኛል።

0 comments:

Post a Comment