በልጆች ላይ የድህነት ውጤት
በልጆች ላይ የድህነት ውጤት በአእምሮ ሕመም ምክንያት የልጅነት ሁኔታ ከጄኔቲክ እና ከአካባቢያዊ ሁኔታዎች ጋር ባለው ትውከት መካከል የሚፈጠር መጫወቻ ውጤት ነው። በተለዋዋጭ ገጠመኞች እና በልጅነት ዲስኦርደር መካከል ያለው ግንኙነት ውስብስብ ሲሆን ከልጆች ጋር የጋራ ውጤት ያመጣል ከድህነት እና ከጤንነት ጋር ተያያዥነት ያላቸው የተራቀቁ የምርምር ተቋማት፣ ዝቅተኛ ገቢን ከሚያስከትሉ የሽምችት ሁኔታዎች እና ድቅተኛ ውጫዊ ድጋፎች ህፃናትን ለአደጋ የተጋለጡ ውጥረትን እና የህይወት ቀውሶችን ያስፋፋሉ፤ እናም በልጅነት ጊዜ የስነ-ልቦና መዛባት ሊያስከትል ይችላል። በጣም ድሃ በሆኑት ቤተሰቦች ውስጥ የሚገኙ ህጻናት የልጆቻቸው የአእምሮ ህመም የመያዝ ዕድሉ በሦስት እጥፍ ይጨምራል (የጤና መምሪያ 1999). ድህነት እና ማህበራዊ አለመምህር በልጆች ግንዛቤ እና የትምህርት ክንዋኔዎች ውስጥ ጉድለት ጋር በእጅጉ የተጎዳ ነው (ዳንካን እና ብሩክስ-ጋን, 1997)። በባሕርይ ጎራ ውስጥ፣ በቤተሰብ ከድህነት ጋር ሁከትና ትኩረት-ያለመረጋጋት መታወክ ምግባር እና ይህ በጣም የማያቋርጥ የኢኮኖሚ ውጥረት ትይዩ ቤተሰቦች ውስጥ ልጆች ምልክት ነው። በድህነትና በልጅነት በሽታ መካከል ያለው ግንኙነት ከሴቶች ይልቅ ለወንዶች ይበልጥ የተለጠጠ ይመስላል፤ እናም በጉርምስና ዕድሜ ላይ ከልጅነት ይልቅ ጠንካራ ይመስላል። የልጅነት የሁከት ተመኖች የተለያዩ ሰፈሮች እና ማህበረሰቦች ውስጥ ይለያያል። በእንግሊዝ አገር ውስጥ የቅድመ ጥናት ውስጣዊ-ከተማ አካባቢዎች ውስጥ የሁከት አደጋዎች ሁለት ትንንሽ ከተሞች (Rutter et al, 1975) ውስጥ ሰዎች ነበሩ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህ መልካም ምግባር መታወክ ሶስት እስከ አራት እጥፍ የበለጠ የተለመደ ዝቅተኛ ገቢ, ወይም በድሆች መንደር ውስጥ የሚኖሩ ጋር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የቀረባቸው ቤተሰቦች ውስጥ የሚኖሩ ልጆች ውስጥ እንደሆነ የታወቀ ነው። ድሃ ልጆችን በከፍተኛ ደረጃ የስነ አዕምሮ ሕመም እንዳይኖር የሚያደርጉት ዘዴዎች በዋናነት በአደጋው ላይ ከሚመጡት ኢኮኖሚያዊ ድክመት ይልቅ የወላጅና የአገልግሎት ባህርይ መጨመር ጋር ተያይዞ ሊመጣ ይችላል። ኢኮኖሚ ከኪሳራ ጋር በተያያዘ የማያቋርጥ የድህነት መለየት አለባቸው፤ ለማያቋርጥ ድህነት የተጋለጡ ልጆች ጉልህ የልጅነት መንፈስ ጭንቀት ምልክቶች (internalizing) እንዳሉባቸው ይገምታል። ልክ የአሁኑ ድህነት እንዲህ የልጅነት ባህሪ መታወክ እንደ ምልክቶች (externalizing) ይተነብያል፣ በአንጻሩ፣ ድህነት በወላጆች ላይ ውጥረት እንደሚፈጥር እና ይህም የቤተሰብን መደበኛ ያልሆነ ማህበራዊ ቁጥጥርን ያግዳቸዋል፤ በአስቸጋሪው የወላጅነት አደገኛ ሁኔታን እና ወላጆቻቸው የልጆቻቸውን ፍላጎቶች ለማሟላት የሚያስችላቸውን ተፅእኖ ይቀንሳል።
ካፕላን et (2001) አል እናቶች እና እያንዳንዱ ዘሮቻቸው በባሕርይውና የግንዛቤ እድገት አስተዋጽኦ አባቶች ጋር የልጅነት ኢኮኖሚያዊ ቦታ እና የግንዛቤ ተግባር ተመልክቶ በልጅነት የበለጠ ትምህርት ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ቦታ በሁለቱም በጉልምስና ውስጥ የግንዛቤ ተግባር ጋር የተያያዙ ናቸው የሚል መደምደሚያ ላይ ተደርስዋል። የመረዳት ችሎታ. በሁለቱም ወላጆቻቸው ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች እና ለልጆቻቸው ትምህርታዊ መሻሻል ማጎልበት (ካግኒቲቭ) ተግባርን ማጠናከር እና በህይወት ውስጥ የመጓዝ አደጋን የመቀነስ አጋጣሚን ሊቀንስ ይችላል። አስቀያሚ፣ አስፈሪ እና አደገኛ እገዳ፣ ቁጥጥር አለመስጠትና ደካማ ወላጅ-የልጆች አባሪነት የድህነትን እና ሌሎች መዋቅራዊ ተፅእኖዎችን ያመጣል። እጅግ በጣም አስፈላጊው ድህነት፣ እኩልነት እና የአእምሮ ጤና በካምብሪጅ ጥናት ላይ በሳይካትሪ ህክምና (2004)፣ ጥራዝ የልጅ-ድንገተኛ ወንጀል ገጠመኞች ድህነት (ፋረንተን፣ 1995)።
በተጨማሪም ድህነት በእናቶች ትምህርት እና የጨቅላ ህጻናት ባህሪ ቁጥጥር ሥር (ፓጋኒ et al, 1999) ላይ በሚደርስበት ጊዜ በአካዴሚያዊ ውድቀት እና እጅግ በጣም ጥፋተኛ ላይ ተጽዕኖ አሳድሯል Eyler & Behnke (1999)። በተለመደው ጊዜ ውስጥ የአደገኛ ዕፆች አግባብ ባልሆነ የአደንዛዥ እጽ ልምዶች የተጋለጡ ህፃናት በሁለተኛ 2 አመታት ውስጥ ውጤቱን ያጠናሉ እና በድህነታቸው በሚኖሩ ህፃናት አደንዛዥ ዕፅ ያስከተለው ውጤት እየጨመረ መሆኑን ደምድመዋል።
በልጆች ውስጥ ስሜታዊ ድህንነትን ለመፍጠር
የልጆች ስብዕና እና እድገት የተስተካከለና የተሟላ እንዲሆንና መልካም ስነ ምግባራቸውን ጠብቀው እንያድጉ ከፍተኛውን ሚና የሚጫወቱት ወላጆች
ናቸው። ወላጆች ለልጆቻቸው ከሚስጧቸው ምድራዊ ሃብት የበለጠ ስሜታቸው የተረጋጋና በራቸው የሚተማመኑ ልጆች እንዲሆኑ ማድረግ ከሁሉም ስጦታቸው የበለጠ ነው ብዬ አምናለሁ። ወላጆች በሚገባ የወላጅነት ሥራቸውን ካላከናወኑ ልጆቹ
የሚቀርጽዋቸው የራሳቸው የእድሜ የትምህርት ቤት ወይም የመንደር ግዋደኞቻቸው ይሆናሉ። የልጆችን መልካም አስተዳደግ ለማረጋገጥ ቤተሰብ ወይም ወላጆች፣ አሳዳጊዎችና ህብረተሰቡ በቅድሚያ በቂ ግንዛቤና እውቀት ሊኖራቸው ይገባል ከጐጂ ለማዳዊ ድርጊቶችና የህዋላ ቀር ባህል የተጠበቁና ጤናማ ልጆችንን ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት ውስጥ አስተዋፅኦ ከአሳዳጊዎችም
ሆነ ከህብረተስቡ ደጋፍ መስጠት ይጠበቅባቸዋል።በልጆች ላይ በትምህርት ቤቶች ውስጥ፣ በመኖሪያ አካባቢያቸው፣ በቤተሰባቸውና በቅርብ ዘመዶቻቸው የስነ ልቦናዊና አካላዊ ጉዳዮች ይደርሱባቸዋል።
ከሁሉም የከፋው ጉዳት ደግሞ ስነ ልቦናዊ ጉዳት ነው።
“ጩኸትና ስድብ ሁሉ .
. . ከእናንተ መካከል ይወገድ።” ኤፌሶን 4:31 ምን ማለት ነው? ችግር ያለባቸውም ሆኑ የተሳካላቸው ቤተሰቦች አለመግባባት ያጋጥማቸዋል። ይሁን እንጂ የተሳካ የቤተሰብ ሕይወት ያላቸው ቤተሰቦች ስለተነሳው አለመግባባት ሲወያዩ የሽሙጥ ንግግር፣ ስድብና ሌላ ዓይነት የዘለፋ አነጋገሮችን አይጠቀሙም። እያንዳንዱ የቤተሰብ አባል ለራሱ እንዲደረግለት የሚፈልገውን ነገር ለሌላው ያደርጋል። ማቴዎስ 7:12። አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው? ቃላት አውዳሚ ውጤት የሚያስከትሉ የጦር መሣሪያዎች ሊሆኑ ይችላሉ። አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሳሌ “ከጠበኛና ከቁጡ ሴት ጋር ከመቀመጥ በምድረ በዳ መቀመጥ ይሻላል” ይላል። (ምሳሌ 21:19 ) እርግጥ ነው፣ ይህ ምሳሌ ጠበኛ ለሆነ ባልም ይሠራል። በተጨማሪም መጽሐፍ ቅዱስ ልጆችን ማሳደግን በሚመለከት “ቅስማቸው እንዳይሰበር ልጆቻችሁን አታበሳጯቸው” ይላል። (ቆላስይስ 3:21) ሁልጊዜ ነቀፋ የሚሰነዘርባቸው ልጆች ወላጆቻቸውን በጭራሽ ማስደሰት እንደማይችሉ ሊሰማቸው ይችላል። እንዲያውም ወላጆቻቸውን ለማስደሰት ጥረት ማድረጋቸውን ከናካቴው ሊያቆሙ ይችላሉ።
ይህን ለማድረግ ሞክር፦ ለሚከተሉት ጥያቄዎች መልስ በመስጠት በቤተሰብህ ውስጥ መከባበር ይታይ እንደሆነ ገምግም።
▪ በቤተሰቤ ውስጥ አለመግባባት ሲነሳ አብዛኛውን ጊዜ አንደኛው የቤተሰብ አባል ተናዶ ቤቱን ጥሎ ይወጣል?
▪ የትዳር ጓደኛዬን ወይም ልጆቼን ሳነጋግር “ደደብ” ወይም “የማትረባ” እንደሚሉት ያሉ የስድብ ቃላትን መጠቀም ይቀናኛል?
▪ ያደግኩት በሚሰዳደቡ ሰዎች መካከል ነው? ቁርጥ ውሳኔ አድርግ። በአነጋገርህ አክብሮት ማሳየት የምትችልባቸውን አንድ ወይም ሁለት መንገዶች አስብና እንድትሠራባቸው ግብ አውጣ። (በንግግርህ ውስጥ “አንተ” ወይም “አንቺ” በማለት ፈንታ “እኔ” እያልክ ለመናገር ቁርጥ ውሳኔ አድርግ። ለምሳሌ ያህል፣ “አንቺ ሁልጊዜ . . .” ከማለት ይልቅ “እንዲህ ስትዪኝ ይከፋኛል” በል።)
ስላወጣኸው ግብ ለትዳር ጓደኛህ ለምን አትነግራትም? ከዚያም ከሦስት ወራት በኋላ ምን ያህል ለውጥ እንዳደረግህ ለማወቅ ጠይቃት።
ከልጆችህ ጋር ስትነጋገር የስድብ ቃላትን እንዳትጠቀም የሚረዱህን አንዳንድ መንገዶች አስብ።
ልጆችህን አመናጭቀሃቸው ወይም በሽሙጥ ተናግረሃቸው ከነበረ ለምን ይቅርታ አትጠይቃቸውም?
ቁንጥጫ፣ በአለንጋ መግረፍ፣ ሌሎች ጎጂ ቅጣቶች በልጆቹ አካል ላይ የሚታዩ ቢሆኑም የስነ ልቦናዊነታቸው ጠባሳ ከሁሉም የበለጠና እጅግ የከፋ ነው፤ በዚህም ምክንያት ልጆቹ ከቤተሰብ ሽሽት፣ ጐዳና ተዳዳሪነትን መምረጥ እና ከሀገር መኮብለልን አማራጭ አድርገው ይወስዱታል። ልጆች የጎዳና ተዳዳሪ የሚሆኑት በድህነት አለንጋ የሚገረፉት ወይም ስብሳቤ የሌላቸው ልጆች ብቻ ወላጆች/ በአስዳጊዎቻቸው የተጎዱ ልጆችም ለዚሁ አደጋ የተጋለጡ ይሆናሉ። ወላጆች ለጆቻቸውን እነርሱ ባደጉበት አስከፊ መንገድ ለማሳደግ ሲሞክሩ ልጆቻቸውን ከጉዳት ከማትረፍ ይልቅ ለአደጋ ያጋልጥዋቸዋል እነርሱም በድርጊታቸው አተርፍ ባይ አጉዳይ ሆነው ይገኛሉ።ልጆቹ ለሚያቀርቡት ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ አለመስጠት ስነ ልቦናቸውን ክፉኛ ይጐዳዋል፤ ማንቋሸሽና ማዋረድም የልጆቹ አእምሮ እንዲረበሽና መልካም አመለካከት እንዲኖንቸው አያደርግም፤ ቸልተኛ
አያያዝም ቢሆን የልጆችን እንክብካቤ የሚቀንስ በመሆኑ ለአካላዊ ጉዳይ ሲዳረጉ ይስተዋላል።የወላጆች ቸልተኛ አያያዝ ልጆቹንን በትኩረት ካለመከታተል የሚመነጭ ሲሆን ልጆቹ በእሳት ሊቃጠሉ፣
ውሃ ውስጥ ሊገቡ፣ ጉዳት ሊደርስባቸውና ከከፋም አስከ ሞት ሊዳረጉ ይችላሉ። የልጆቹን ክብር ዝቅ ማድረግ ደግሞ ሌላው ስነ ልቦናዊ ቅጣት ነው። ይህም በራሳቸው እንዲያፍሩና እንዲሸማቀቁ ያደርጋቸዋል።በአካላቸው ላይ በሚፈፀምባቸው ቅጣት ሳቢያ ልጆቹ የመድማት፣ የመቁሰል፣ አካላዊ እብጠት፣ ለረጅም ጊዜ የሚቆይ ጠባሳና ምልክት፣ አዝጋሚ የሆነ አካላዊ እድገት፣ አካል ጉዳተኝነትና ሞትን ያስከትላሉ፡የልጆች በስነ ልቦናቸው ላይ ጉዳት ሲደርስባቸው ጥሩ ያልሆኑ የባህሪ ለውጦች ይስተዋልባቸዋል
ይህም የምግብ ፍላጐት መቀነስ መነጫነጭ፣ ተደጋጋሚ ህመሞችና በሌሎች ምልክቶች ሊገለፅ ይችላል፡፡በራሳቸው ላይ ያላቸው እምነትም ይሸረሸራል፡፡
በቤተሰቦቻቸው ወይም በአሳዳጊዎቻቸው ላይም ማመፅ ይጀምራሉ።ልጆች ሌሎችን የመቅረብና የማመን ከፍተኛ ስሜት አላቸው፤ ስነ ልቦናቸው ከተነካ ግን ሰዎችን የመቅረብና የማመን ሁኔታ ፈፅሞ አይስተዋልባቸውም፡
የድባቴ ስሜትም አላቸው። የትምህርት ውጤታቸውም እየቀነሰ ይሄዳል፡፡
ባሉበት ሁኔታ ውስጥም ያለመረጋጋት ፀባይ የሚታይባቸው ከመሆኑም በላይ የአዕምሮ ዘገምተኝነትም
ሊከሰትባቸው ይችላል፡፡ልጆቹ
በእነዚህ ችግሮቻቸው ሳቢያ ማህበራዊ ቀውስ ሲፈፅሙ ይታያሉ፡፡መገለል፣ ትምህርት ማቋረጥ፣ መኮብለል፣ የአልኮልና
አደንዛዥ ዕፅ ተጠቃሚና ተጠቂ ይሆናሉ፡፡ወደ ጐዳና ህይወት የሚቀላቀሉትም ብዙዎች ናቸው። ከዚያም ወንጀል መፈፀም፣ ህግንና ህግ አስከባሪ አከላትን ያለመቀበልና ጥቃት ማድረስ የመሳሰሉት ፀረ ማህበራዊ ባህሪያትን ለማሳየት በህብረተሰቡ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ እንዲደርስ ያደርጋሉ።ድህነት ጉዳት ሊያስከትሉ ከሚችሉ የልጆች ቅጣትና አያያዝ መንስኤዎች መካከል ቅድሚያውን ይይዛል።ልጆችንን የንዴት ማብረጃ መንገድ በማድረግ አላስፈላጊ ቅጣቶች ይቀጣሉ፡፡
ማህበራዊ አገልግሎት ያለመኖሩም በልጆቹ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ያሳድራል፡፡
በህብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ያላቸው ተገቢ ያልሆኑ የልጆችን አስተዳደግና የስነ ምግባር መገንቢያ ናቸው ተብለው የታመነባቸው የተለያዩ ዘይቤዎች ይገኛሉ፡፡
ከእነዚህ መካከል የህብረተሰቡን ኋላቀር የሆነ ባህል፣ ወግ፣ ልምድና የአኗኗር ዘዴዎች ይጠቀሳሉ፡፡አማራጭ የመልካም ስነ ምግባር መገንቢያ መንገዶች ላይ የሚስተዋለው የግንዛቤ እጥረትም ሌላው
ችግር ሲሆን ከፍተኛ የቤተሰብ ቁጥር እና ያልተመጣጣነ የቤተሰብ ቁጥር ለችግሩ መፈጠር መንስኤ ነው፡፡ወላጆች ችግሮችን የመቋቋም ችሎታቸው የቀነስ ከሆነ በልጆቻቸው ላይ ተፅእኖ ይፈጥራሉ፡፡ተከታታይ የቤተሰብ ቀውስ ማለትም የትዳር መፍረስ ሊሆን ይችላል ልጆች እንዲጐዱ ያደርጋል ወላጆች
በልጆች አስተዳደግ ዙሪያ ያላቸው ግንዛቤ ከራሳቸው የአስተዳደግ ምንጭ የመነጨ በመሆኑ ልጆቻቸውን እነሱ ባለፉበት የአስተዳደግ መስመር እንዲየልፉ በሚጥሩበት ወቅት ህፃናቱ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ እንዲፈጠርባቸው ያደርጋል። የወላጆች የግል ባህሪ ቁጡ ከሆነ ይህንኑ ባህሪያቸውን መቆጣጠር ሳይችሉ የሚቀሩ ከሆነ ብሶትና ብስጭታቸውን በልጆቹ ፊት ወይም በልጆቹ ላይ ይፈፀማሉ። ልቅ የሆነ አስተዳደግም ለቁጥጥር አመቺ ስላልሆነ የልጆቹ አስተዳደግና ባህሪያቸው ከመስመር አንዲስት ያደርጋል።የልጆች
ስነ ምግባር አስተማማኝ ደረጃ ላይ እንዲደርስ የልጆችንና ወላጆች ግንኙነት በመከባበር ላይ የተመሰረተ ሊሆን እንደሚገባ ይመከራል፡፡
በመነጋገር ማመን፣ የልጆቹን ተፈጥሮአዊ ራስን የመቆጣጠር ብቃት የሚያዳብር ችሎታ ማዳበር እንዱችሉ ማድረግም ከቤተሰብ ይጠበቃል፡፡
ልጆች ያሏቸውን አማራጮች በማቅረብ እንዱወስኑ አሊያም እንዲመርጡ ማድረግ ውሳኔ ሰጪነታቸው
እንዲበለፅግ ያደርጋል፡፡ መልካም ስነ ምግባሮቻቸውን ማድነቅና ማበረታታትም ተገቢ ነው፡፡ሲሳሳቱ እንደማስተማሪያ እንጂ እንደውድቀት መለኪያ አድርጐ መመልከት አሉታዊ ተፅእኖ አለውና በስህተታቸው እንዲማሩበት ማድረግ ይገባል፡፡ወላጆች ለልጆች የሚያስተምሯቸውን እሴቶች ማክበር አለባቸው፡፡በመካከላቸው ያለው ግንኙነቶች ነፃና ክፍት መስመርን የሚያበረታታ መሆን አለበት፡፡በምንም አይነት መልኩ አዋራጅና ህፃናቱን ዝቅ የሚያደርጉ አያያዞች መታየት የለባቸውም፡፡ልጆቹን ሆን ብሎ ማናደድና ማነፃፀርን በማስወገድ ግንኙነቱን ጤነኛ ማድረግ ይቻላል።ወላጆችና አሳዳጊዎች ለልጆቹ ከፍተኛ ትኩረት መስጠት ይኖርባቸዋል። በቂ እረፍት እንዲየገኙ ማድረግ፣ ከልጆች ጋር አብሮ ጊዜን ማሳለፍ፣ በልጆች መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በጊዜው መፍታት፣ ልጆቹን በተለያዩ ድርጊቶች ውስጥ ማሳተፍና የተለያዩ የማበረታቻ ሽልማቶችን መስጠት የልጆቹን አእምሮ ብሩህ ያደርጋልና ተፈፃሚ መሆን አለባቸው።የስሜት ደህንነቱ የበለጠ የተጠበቀ እንዲሆንለት የማይፈልግ የስው ልጅ የለም። ስሜታዊ ድህንነት አንድ ስው ስለራሱ የሚስማው ስሜት ነው። ከሌሎች ጋር ባለው ግንኙነት ጥሩ ስሜት የሚስማው ከማን ጋር (ለምሳሌ ከቤተብ ጋር) ነገሮች መልካም በሆኑ ጊዜ የሚስማውንም ስሜት አመኔታውንም ያካትታል። አንዳንድ ጊዜ መጥፎ ገጠመኞቻቸው የተነሳ
ስዎች በእነዚህ አካባቢ የሚስማቸው ስሜት አመኔታ የጎደለው ሊሆን ይችላል።በቤተስብ ውስጥ ወላጆች አጥብቀው መስራት ያለባቸው የልጆቻቸው የስሜታቸው ድህንነት የተጠበቀ እንዲሆን
መሆን ይገባዋል። በአብዛኛው በቀላሉ የሚረበሹና
አሉታዊ ጠባዮች የሚያሳዩትን ልጆች ለመረዳትና ወደ ጤናማ ጠባይ ለማምጣት የሚቻለው የልጁን ስሜትዊ ድህንነት ተረድቶና ጠብቆ
ወደ ተሻለ ደረጃ ማምጣት ነው። ይህ ዘዴ የሚስራ ሆኖ ሳለ በሥራ ይተርጎም ሲባል በሥራ ለሚተረጉመው ግን ቀላል ሆኖ አይገኝም።
1. የሚስራውና ስኬታማ ውጤት ያስመዘገበው ዘዴ እንዲህ ነው፤ በየማታው ከ3 እስከ 5 ደቂቃ ለልጁ ብቻ ጊዜ መመደብ፣ ከዚያም ልጁ ወደ መኝታ እንደሄደ እናት ወይም አባት ተራ በተራ በተኛበት ቦታ ሄደው የልጁን መኝታ ቤት መብራት ጠፍቶ እያለ በልጁ የአልጋ ጫፍ ላይ መቀመጥ። ልጁ አሁን በመኝታ ክፍሉ በአልጋው ላይ እያለ የወላጁን እጅ ይዞ በአይን መታያየት ሳይኖር መብራቱ ከመጥፋቱ የተነሳ ሳይተያዩ ወላጁ ለልጁ ስላሳለፈው ቀንና የሆነውን ነገር ይነግረዋል፤ ወላጅ ይህንን ሲያደርግ ልጁን ጥያቄዎች አያነሳበትም ወይም እንዲናገር አይጠይቀውም። በዚህን ጊዜ ልጁ ወላጁ የደረስበት ለማንኛውም ስው እንደሚደርስ ሲረዳና ሲያውቅ ልጁ በትምህርት ቤት ስላሳለፈው ቀን መናገር አይከብደውም እንደውም የስሜት ጫና ካለው ለወላጁ መናገር ይጀምራል።
2. ልጁ ለወላጁ የሚናገረው (ለምሳሌ ትምህርት ቤት መሄድ እጠላለሁ) የሚል ከሆነ ወላጅ በችኮላ ልጁ የበለጠ እንዳይናገር መዝጋት ወይም መንቀፍ የለበትም። ወላጅ ነቀፋውን ማቆየትና ልጁ ለምን ትምህርት ቤት መሄድ እንደጠላ ለመጥላቱም መነሻ የሆነው ነገር ማወጣጣት ይኖርበታል ግልጽ እንዲያደርገው። አንደኛው ዘዴና የሚስራው ስለትምህርት ቤት መሄድ የጠላበትን መነሻ ካልተናገረ ዘዴው ወላጅ ልጁ ስላመጣው ሃሳብ በጥያቄ መልክ እንደገና ወደ ልጁ መመለስ ነው (ለምሳሌ. ትምህርት ቤት መሄድ ጠላህ እንዴ?) የጠላኸው ማንን ነው? ትምህርት ወይስ አስተማሪዎቹን? አስተማሪዎቹን ሁሉ ነው የጠላኸው? አይመስለኝም ምናለባትም መምህር ዘውዴቱን? ወዘተ.
3. ለትናንሽ ልጆች “ለምን” የሚለው ጥያቄ ቢነሳላቸው መልስ የሚስጡት መልስ ላይኖር ይችላል። አንዳንድ ጊዜ ትናንሽ ልጆች የሚስጡት መልስ አጥጋቢ አይሆንም ወይም መልስ የሚስጡት ያጣሉ። ስለሆነም ወላጆች “ለምን” የሚለውን ጥያቄ ባይነሱ ይመረጣል።
4.
ወላጆች ማስወገድ ያለባቸው አሉታዊ ቃሎችን (ዓይደለም ወይም ስህተት ነው የሚለውን) በተለይም ልጁ በሚያንብበት ጊዜ፣ ከዚህ የተሻለው ምርጫ “ወደ ትክክሉ ተቃርበሃል” ወደ ትክክሉ ተቃርበሃል የመሳስሉት ቃላት ልጁ ለማንበብ ፍላጎቱ እንዳይከስምና ስሜቱ ለማንበብና
ለመማር ፍላጎት እንዲነሳሳ ይረዳዋል፤ ያለበለዚያ ግን ልጁ የሚታየው ውድቀቱ ብቻ ይሆናል።
5. ወላጆች
ለልጆቻቸው መንገር ያለባቸው ልጆች ባንዳንድ ነገሮች ችሎታ እንዳላቸው ጥሩ ልጆችም እንደሆኑና እንደሚወደዱም ከወላጆቻቸው መስማት ለስሜታቸው ድህንነት
አስተዋጽኦ ያደርጋል።
ወላጆች ልጆቻችንን ወድቀታቸው ላይ ብቻ አተኩረን ከነገርናቸው መልስው እኛኑ ያስቸግራሉ ወይም ይረብሻሉ። እኛም ወላጆች ልጆቻችን ሲረብሹን ስለነርሱ መልካም ነገር መናገር ያቅተናል።
ከዚህ የተነሳ ልጆች ሁልጊዜ ትክክል እንዳልሆኑ ከወላጆቻቸው ከስሙ ውሎ አድሮ ስለራሳቸው ያላቸው አመለካከት አነስተኛ ስለሆነ የስሜታቸው
ድህንነት ያንኑ ያህል ይነካል።
6. ቀኝእጃቸውን የሚጠቀሙ ልጆች በቀኝ ጎናቸው ወይም በሆዳቸው መተኛት አብረውም ጭንቅላታቸውን ወደ ግራ
ትከሻቸው ማዞር ይቀናቸዋል።
ግራኝ ልጆች ደግሞ በጠቅላላው ሲተኙ ጭንቅላታቸውን ወደ ተቃራኔው ወገን ያዞሩታል። ወላጆች የልጃቸውን አልጋ አቀማመጥ ተፈጥሮአዊ ወደሆነው አቅጣጫ (እንደ እጃቸው አጠቃቀም ማለትም ግራኞች ወይም ቀኞች) ፈታቸው ወደ ግድግዳው ትይዩ በማድረግ መዘርጋት ይኖርባቸዋል።
(በቁጥር 6) እንደዚህ አይነቱ አስተኛኘትት ለልጁ የደህንነት ስሜት እንዲስማው ከማድረጉም ሌላ
ልጁ በለሌት ሽንት በመኝታው ላይ እንዳይሽናና ከለሊት የቅዠት ስሜት እንዳይቸገር ይረዳል ተብሎ ይታመናል።የልጁን አልጋ የተዘረጋው በቤቱ ውስጥ በቀኝ መአዘን ላይ ከሌላው ክፍል ጋር የተያያዘ ሥፍራ ከሆነ በእንቅልፍ ጊዜ እረፍት የማይስማው ልጅ ከሆነ እንዲህ አይነቱን ሥፍራ አይፈልገውም ምክንያቱም በመኝታው ጊዜ ደህንነት አይስማውም።
7. ልጁ በመኝታው ጊዜ መብራት ያስፈለገው እንደሆነ ስማያዊ ወይም አረንግዋዴ አቦል ከቀይ አቦል የተሻለ ስለሆነ ወላጅ ይህንኑ ቀለም መምረጥ ይኖርበታል ምክንያቱም ስማያዊ አረንግዋዴው ስሜቱን የሚያረጋገው ቀለም ሲሆን ቀዩ ደግሞ ብርሃኑ ስሜቱን የሚቀስቅስ ስለሆነ እንቅልፍ የሚነሳው ይሆናል ማለት ነው።
8. ወላጆች ስለልጆቻቸው እውነት የሆነውን የስሜታቸውን ገጽታ መቀበል መቻል አለባቸው።
ልጃቸው በአንድ ነገር የሚደነግጥና የሚፈራ ፍርሃቱም በወላጁ ዘንድ ተቀባይነት ባይኖረውም እንክዋን የልጁ እውነተኛው ስሜት ይህ ስለሆነ ወላጁ የልጁን ስሜት መቀበል ይኖርበታል። የልጁን ስሜት ባለምቀበል ከመተችት ይልቅ የልጁን ስሜት በወቅቱ መጠየቅና ከዚህ ከሚስማው ስሜት የሚወጣበትን መንገድ ወላጆች
የልጁን ጭንቀት ወይም ፍርሃት ለመቀነስ ለመርዳት ጥረት ማድረግ
ይኖርባቸዋል።
9. ወልጆች በተከታታይ የተወስኑ ደቂቃዎች (10 ደቂቃዎች) በመውስድ ለልጆቻቸው ትኩረት
በመስጠት ስለልጆቻቸው ለማወቅም ሆነ ለመረዳት ህሳቤ እንዲኖራቸው ይረዳቸዋል።
10.
ወላጆች ለልጆቻቸው ማንበብ ይጠበቅባችዋል። ጨቅላ ልጆች እድሜያቸው (2-6) ክልል ውስጥ የሆኑት ከሚወድዋቸው የልጆች መጻህፍት የተነበብላቸውን ታሪክ በመድገም መልስው ለራሳቸው ያነቡታል። ከፍ ያሉት ልጆች እድሜያቸው (7- 10) ክልል ያሉት ደግሞ ወላጆቻቸው ልጆቹ ከሚወዱት መጻህፍት
መካከል ያነበቡላቸው እንደሆነ ከወላጆቻቸው ጋር ልጆቹ አንድ አይነት ፍላጎት እንዳላቸው እንደሚጋሩ ሆኖ ይስማቸዋል የታሪክ መጻህፍትና ከኢንሳክሎፒዲያ ታሪኮች የመሳስሉትን ማለት ነው።
11. ከልጆች ጋር ጊዜ ወስዶ መጫወት ልጆቹም አዋቂዎች መጫወትና መሳቅ እንደሚችሉ ለማሳየት ልጆችን ለማስተማር ይረዳል
12.
በወላጆች ዘንድ መመሪያን በመስጠት ተከታታይነት ወይም ያለመወላወል ዋነኛና አስፈላጊ መሆን አለበት። ወላጆች መመሪያ በመስጠቱ በኩል ተከታታይና የማይወላውሉ ከሆኑ ልጆችም ሥፍራቸው የት እንደሆነ ያውቃሉ። ወላጆች መመሪያን በመስጠት ተከታታይና የሚወላውሉ ከሆነ ልጆች የሚከተሉት አቅጣጫ የትኛው እንደሆነ ስለማያውቁ ስለሚዘበራረቅባቸው ልጆቹም ስሜታቸውና ሃሳባቸው የማይቸበጥ ያደርገዋል። ከዚህ ሁኔታ ለመዳን ወላጆች ያሉትን ማድረግ ይኖርባቸዋል ቅጣት ካሉ መቅጣት ሽለማት እንስጣለን ካሉ ያሉትን ማድረግ ማለት ነው።
ያለበለዚያ ወላጆች በልጆቻቸው ዘንድ ያላቸው ተቀባይነት በጥያቄ ላይ ይሆናል። ይህ ሁኔታ በወላጆችና በልጆች መካከል መፈጠሩ ለወደፊቱ የልጆቻቸው አስተዳደግ
ሥራ ለወላጆች አስቸጋሪ ያደርግባቸዋል።
አባትም እናትም በስራ ላይ ሳሉ ልጅ ሰለማሳደግ
አባትና እናት ሁለቱም ወላጆች በስራ ላይ ሆነው ለቤተሰብና ለስራ ጊዜአቸውን ማመጣጠን አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል። የቤተሠብና የልጆችን ፍላጎት ግምት ውስጥ በማሰገባት በጥንቃቄ ማሰብና ፕላን ማውጣት ጠቃሚ ነው። ይህም ከሥራ ብዛትና ከቤተሠብ አኗኗር ጋር በተገናኘ መልኩ የሚመጣን ጭንቀት ሊያስወግድ ይችላል።
ወላጆች ሥራ ላይ በሚሆኑበት ጊዜ ጥሩ መዋለህፃናት በጥንቃቄ መምረጥ በጣም ጠቃሚው ነው። ለትምህርት እድሜአቸው ያልደረሱ ልጆች ካሉ ለወላጅና ለልጆች የሚስማማ መዋለህፃናት መምረጥ በጣም ወሳኝ ነው። ለትምርህት የደረሱ ልጆች ካሉ ከትምህርት ሰዓት በፊትና በሁዋላ የሚቆዩበት ስፍራ ይፈልጉ ይሆናል። ብዙ አይነት ልጆች የሚቆ በትና እነክብካቤ የሚያገኙበት ስፍራ ያገኛሉ። በተለይም እድሜአቸው ለትምህርት ያልደረሱ ልጆች ከዘመዶቻቸው ጋር ፤ከግለሰቦች ጋር ቤትን በመሰለ አከባቢና በተለያዩ የመንከባከቢያ ማእከሎች መቆየት ይችላሉ።
አባትና እናት በጋራ ሆነው ለልጆቸቻው መዋለህፃናት ለመምረጥ መሞክር አላባቸው። ከመዋለህፃናት ወይም ከትምህርት ቤት ማን እንደሚያደርሳቸውና ማን እንደ ሚመልሳቸው መታሰብ አለበት። የስራው ጸባይ በተለያየ ጊዜ መውጣት ማን እንደሚያስችለው መነጋገርና ማን የሥራ ሰአቱን ልጆቹ በሚፈልጉት መልክ ማመቻቸት እንደሚችል መነጋገር ያስፈልጋል ። አንድ ወላጅ ብቻ ይህንን ማድረግ የሚችል ከሆነ የሥራ ውጥረቱን ለማገዝ ሌላው ወላጅ ምን መርዳት እንደሚችል መነጋገር ይገባል።
ሁለቱም ወላጆች በሚሠሩበት ጊዜ የታመሙ ልጆችን መንከባከብ ትልቅ ጭንቀት ሊያሰከትል ይችላል። ልጆች መታመማቸው የማይቀር ነው። አንድ ወይም ሁለት ከፍያሉ ጎልማሳ ሰዎች ምናልባትም ዘመድ ወይም የቤተሠቡ አባል ልጆቹ በሚታመሙበት ጊዜ እንዲንከባከቡ ተጠባበቂ ማኖር በጣም ጠቃሚ ነው።
ሁለቱም ወላጆች በሚሠሩበት ጊዜ እያንዳንዱ ወላጅ እኩል ልጆቹን መንከባከብና የቤትን ስራ እኩል መሥራት ያስፈልጋል። ሁለቱም ቤተሠቦች በጋራ ጊዜያቸውን በአንድላይ ማሳለፍ፣ በግልም፣ እነድቤተሠብም ጊዜን ማሳለፍ ያሰፈልጋል ልጆች ቤተሠቡ አባል የመሆናቸው ስሜት እንዲሰማቸውና ወላጆቻቸው መጠን በሌለው መልኩ እነደሚያፈቅሯቸው እንዲሰመቸው ያስፈልጋል።
ሁለቱም ወላጆች በሚሠሩበት ጊዜ የቤት ውስጥ ስራን መጋራት ጠቃሚ ነው።የቤት ውሰጥ የዘወትር ሥራ የአንድ ወላጅ (የአባት ወይም የእናት) ሃላፊነት ነው ብለን ከአሰብን ቅሬታን እያከማችን እንመጣለን። በእድሜአቸው ከፍ ያሉት ልጆች የቤትውስጥ ስራን ሊረዱ ይችላሉ፡ በአጠቃላይ ቅዳሜ ጠዋትን ለረጅም ጊዜ በመመደብ የቤት ስራን በመስራት የተቀረውን የሣምንቱን እረፈት ጊዜ ለቤተሠብና ለግል ጉዳዮች መጠቀም ይቻላል።
ሁለቱም ወላጆች በሚሠሩበት ቤተሰብ አንደኛው ወላጅ ልጆቹን በሚነከባከብበት ጊዜ እያንዳነዱ ወላጅ ለራሱ ጊዜ ይፈልጋል። ይህም እነርሱ በሚፈልጉበት ወይንም ሌላ እነቅስቃሴ ወይንም እረፍት በማድረግ ማሣለፍ ያሰችላል።
ሁለቱም ወላጆች በሚሠሩበት ጊዜ እንደባለትዳር አንድ ላይ የሚሆኑበት ጊዜ ማግኘት አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል፡፡ አንዳንድ ቤተሰቦች በዚህን ጊዜ ነው እራሳቸው ከልጆቹ ጋር ከመሆን ፋንታ ልጆቻቸውን የሚጠብቅላቸው ሰው እንደሚያሰፈለጋቸው የሚሰማቸው። ወላጆች አንድ ላይ በመሆን አርስ በርስ የሚደሰቱበትና ጉዳዮቸንና የሚወያዩበት ጊዜ ያስፈልጋቸዋል።
የወጣቶች ጥያቄ
“ከወላጆቼ ጋር ለዓመታት ከኖርኩ በኋላም እንኳ ስለ እነሱ ገና ብዙ ያላወቅኩት ነገር መኖሩ ይገርመኛል። እነርሱ እንኳን ስለራሳቸው መናገር ባይፈልጉም እኔ ግን የበለጠ ለማወቅ ሁኔታዎች እስክሚስተካከሉልኝ
እጠብቅ ነበር ወላጆቼን እነማን እንደሆኑ ሳውቅ በህይወታቸው ያለፉበትን ተሞከሩ ሳውቅ የማገኛቸው አራት ጥቅሞችም እንዳሉ አስተዋልኩ።
1ኛው ጥቅም፦ ስለ ወላጆቼን ለማወቅ መፈለጌ በራሱ ሊያስደስታቸው ይችላል። ስለ እነሱ ሕይወት ለማወቅ መፈለጌ እንደሚያስደስታቸው አያጠራጥርም። ደግሞስ ማን ያውቃል፣ ይህ ሁኔታ ራሳቸውን በኔ ቦታ በማስቀመጥ እኔንም ሆነ ስሜቴን የበለጠ እንዲረዱ ያደርጋቸው ይሆናል!
2ኛው ጥቅም፦ ወላጆቼ ነገሮችን የሚያዩበትን መንገድ የበለጠ እረዳለሁ። ለምሳሌ ያህል፣ ወላጆቼ ቀደም ሲል ዝቅተኛ ኑሮ ነበራቸው? ይህን ማወቄ አሁን ገንዘብ ቆጣቢ መሆናቸው አስፈላጊነቱ ለእኔ ባይታይህም እንኳ እንዲህ ዓይነት ሰዎች የሆኑበትን ምክንያት እንድታውቅ ይረዳኛል።
ስለ ወላጆቼ አስተሳሰብ እንዲህ ዓይነት ማስተዋል ማግኘቴ ጠቃሚ ሊሆን ይችላል። እንደገባኝ
ወይም እንደተረዳሁት “የወላጆቼን አስተሳሰብ ማወቄ አንድ ነገር ከመናገሬ በፊት፣ የምናገራቸው ቃላት በእነሱ ላይ ምን ስሜት ሊፈጥሩ እንደሚችሉ እንዳስብ አስችሎኛል” ብሏል።
3ኛው ጥቅም፦ ስለ ራሴ ሕይወት ሳልሽማቀቅ
መናገር ይበልጥ ቀላል ያደርግልኛል ብዬ አስባለሁ። ለወላጆቼ ስሜቴን አውጥቼ ስነግራቸው ለመጀመሪያ ጊዜ ፍቅር ሲይዛቸው ስለነበራቸው ሁኔታና ያ ስሜት ምን ያህል ደስ የሚል እንደነበር ነገሩኝ።
4ኛው ጥቅም፦ስለወላጆቼ
ማወቄ ትምህርት ይስጠኛል። የወላጆቼ የሕይወት ተሞክሮ እኔ እራሴ የገጠሙኝን
የሚያስጨንቁና ተፈታታኝ የሆኑ ሁኔታዎች ለመቋቋም ሊረዳኝ ይችላል ብዬ አስባለሁ። “ወላጆቼ የተለያየ አካላዊ፣ ስሜታዊና መንፈሳዊ ፍላጎት ያላቸው ሰዎች ያሉትን ትልቅ ቤተሰብ ማስተዳደር የቻሉት እንዴት እንደሆነ ማወቄ “ከእነሱ የማገኘው ጠቃሚ ትምህርትና ተሞክሯቸው ይረዳኛል ብዬ አስባለሁ።” መጽሐፍ ቅዱስም “ጥበብ ያለው በአረጋውያን ዘንድ አይደለምን? ማስተዋልስ ረጅም ዕድሜ ባላቸው ዘንድ አይገኝምን?” የሚል ጥያቄ ያቀርባል።ኢዮብ 12:12
ስለ ወላጆቼ ይበልጥ ማወቅ በፈለኩ ጊዜ ያደረጉት ከዚህ እንደሚከተለው
ነው።
ትክክለኛውን ጊዜና ቦታ መረጥኩ። ጊዜና ቦታው የግድ አስቀድሞ የታሰበበት መሆን አያስፈልገውም። ከዚህ ይልቅ ዘና ብዬ ከወላጆቼ ጋር የምጫወትበትን አጋጣሚ ተጠቀምኩበት።
ከዚህም ቀጥዬ ጥያቄዎች ጠየኩ። ጥያቄዬን ሳቀርብላቸው ግትር ሳልሆን ማለትም ያሉትን ለመቀበል እራሴን ዝግጁ አድርጌ በኔ መንገድ ብቻ መልስ ሳልጠብቅ መቅረብ ማለቴ ነው። ብዙውን ጊዜ ለአንድ ጥያቄ የሚሰጠው መልስ ወደ ሌላ ታሪክ ወይም ርዕስ ሊመራ ይችላል የሚለውንም ሃሳብ በልቤ ይዤ ነበር የቀረብኳቸው። አባቴ በተለይም ንግገርን ማስቀየር
የታወቀ ስለሆነ በጭውውቴ መጀመሪያ ወደተነሳው ርዕስ ለመመለስ ስሞክር የማስረሳቱ ጉዳይ ነበር፤ ጥያቄ ለወላጆቼ ያቀረብኩላቸው
መረጃ መሰብሰብ ብቻ እይደለም ይልቁንም ለራሴ ትምህርት ለማገኘት ስለሆነ
ግቤ ላይ ትኩርት በማድረግ ነበር። የበለጠ ደግሞ ከወላጆችቼ ጋር የበለጠ መቀራረብ ስለነርሱ ለማወቅ አይነተኛው መንገድ ነው፤ ይህን ለማድረግ የሚያስችለኝ ከሁሉ የተሻለው መንገድ ደግሞ እነሱ በሚያስደስታቸው ርዕስ ዙሪያ ማውራት ነው እንደሆነም
ተረድቼአለሁ።
አስተዋይ ሁን። “የሰው ልብ ሐሳብ እንደ ጥልቅ ውሃ ነው፤ አስተዋይ ሰው ግን ከዚያ ቀድቶ ያወጣዋል።” (ምሳሌ 20:5) በተለይ ወላጆችህ መናገር የማይፈልጉትን ነገር እንዲነግሩህ በምትፈልግበት ጊዜ አስተዋይ መሆን ይኖርብሃል። ለምሳሌ ያህል፣ አባትህ በአንተ ዕድሜ ሳለ የፈጸመው የሚያሳፍር ስህተት ምን እንደነበረና እንደገና ዕድሉን ቢያገኝ ሁኔታውን እንዴት በተለየ መንገድ ሊይዘው እንደሚችል ለማወቅ ትጓጓ ይሆናል። ይሁን እንጂ እንዲህ ያሉ ርዕሶችን ከማንሳትህ በፊት “ስለዚህ ነገር ብጠይቅህ ቅር ይልሃል?” ብለህ ብትጠይቅ ጥሩ ነው።
ዘዴኛ ሁን። ወላጆችህ ስለ ራሳቸው ሲነግሩህ ‘ለመስማት የፈጠንክ ለመናገር የዘገየህ ሁን።’ (ያዕቆብ 1:19) ወላጆችህ ያካፈሉህ ነገር ያልጠበቅከው ነገር ቢሆንም አታፊዝባቸው ወይም አትዝለፋቸው። “እንዴ! እኔ አላምንም!” ወይም “በእኔ ላይ ጥብቅ የሆንከው ለዚህ ነዋ!” እንደሚሉት ያሉ አስተያየቶችን የምትሰነዝር ከሆነ አባትህ ወይም እናትህ ተጨማሪ ነገር ሊነግሩህ አይፈልጉም። ወላጆችህ የነገሩህን ለሌሎች ሰዎች መናገርህም ወላጆችህ ይበልጥ ግልጽ እንዲሆኑልህ አያበረታታቸውም።
አሁንም ጊዜ አለህ!
ከላይ የቀረቡት ሐሳቦች ከወላጆችህ ጋር አብረህ በምትኖርበት ጊዜ ከእነሱ ጋር ይበልጥ እንድትተዋወቅ ሊረዱህ ይችላሉ። ይሁን እንጂ አሁን ራስህን ችለህ የምትኖር ከሆነስ? እነዚሁ መሠረታዊ ሥርዓቶች ከወላጆችህ ጋር ከዚህ በፊት ጨርሶ ከማታውቀው ወላጅህ ጋር እንድትቀራረብ ሊረዱህ ይችላሉ። አሁን የሚኖረው ብቻውን ቢሆንም “ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አባቴን ይበልጥ እያወቅኩት ነው፤ ይህ ደግሞ በጣም አስደስቶኛል” ብሏል።
ስለዚህ የምትኖረው ከወላጆችህ ጋርም ይሁን ራስህን ችለህ፣ ስለ ወላጆችህ ለማወቅ አሁንም ጊዜ አለህ። በዚህ ርዕስ ውስጥ የቀረቡትን ሐሳቦች ተጠቅመህ ወላጆችህን ይበልጥ ለማወቅ ለምን አትሞክርም?
ሊታሰብባቸው የሚገቡ ነጥቦች
▪ በዚህ ርዕስ ከተጠቀሱት ርዕሰ ጉዳዮች ውስጥ ወላጆችህን መጠየቅ የምትፈልገው የትኞቹን ነው?
▪ ስለ ወላጆችህ ይበልጥ ማወቅህ ራስህን ይበልጥ ለማወቅ ሊረዳህ የሚችለው እንዴት ነው?
ወላጆችህን እንደሚከተሉት ያሉ ጥያቄዎችን ጠይቃቸው፦
ጋብቻ፦ አንተና እማዬ የተዋወቃችሁት እንዴት ነበር? መጀመሪያ እንድትዋደዱ ያደረጋችሁ ምን ነበር? ከተጋባችሁ በኋላ የኖራችሁትስ የት ነበር?
የልጅነት ሕይወት፦ የተወለድከው የት ነው? ከወንድሞችህና ከእህቶችህ ጋር ትስማማ ነበር? ወላጆችህ ጥብቅ ይሆኑብህ ነበር? ወይስ ልል ነበሩ?
ትምህርት፦ በጣም የምትወደው ትምህርት ምን ነበር? የማትወደውስ ትምህርት የትኛው ነበር? ከሁሉ አስበልጠህ የምትወደው አስተማሪ ነበረህ? እንድትወደው ያደረገህ ነገር ምንድን ነው?
ሥራ፦ የመጀመሪያ ሥራህ ምን ነበር? ትወደው ነበር? ሌላ ዓይነት ሥራ ምረጥ ብትባል ምርጫህ ምን ይሆን ነበር?
የሚያስደስታቸው ነገር፦ በዓለም ላይ ያሉ ቦታዎችን የመጎብኘት አጋጣሚ ብታገኝ የት ብትሄድ ደስ ይልሃል? ምን ችሎታ ቢኖርህ ደስ ይልህ ነበር?
መንፈሳዊ ታሪክ፦ ያደግከው በክርስቲያን ቤተሰብ ውስጥ ነው? ካልሆነ፣ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ለማወቅ ፍላጎት እንዲያድርብህ ያደረገው ነገር ምንድን ነው? ከመጽሐፍ ቅዱስ መሠረታዊ ሥርዓቶች ጋር ሕይወትህን ለማስማማት ከባድ የሆነብህ ነገር ምንድን ነው?
ትልቅ ግምት የሚሰጠው ነገር፦ ለጥሩ ጓደኝነት በጣም አስፈላጊ የሆኑት ነገሮች ምንድን ናቸው ትላለህ? ለደስተኛ ሕይወትስ? ለተሳካ ትዳርስ? በጣም ጥሩ ነው የምትለው ምን ምክር ተሰጥቶሃል?
እንዲህ ለማድረግ ሞክር፦ ከላይ ከቀረቡት ጥያቄዎች ውስጥ ጥቂቶቹን ምረጥና ወላጆችህ ምን መልስ ሊሰጡ እንደሚችሉ ገምት። ከዚያም እነሱን ጠይቃቸውና የሚሰጡህን መልስ አንተ ይነግሩኛል ብለህ ከገመትከው ጋር አወዳድር።
ለወላጆች የተሰጠ ማሳሰቢያ
ከባለቤትሽ፣ ከሴት ልጅሽና ከወዳጆቻችሁ ጋር እራት እየበላችሁ ነው እንበል። በጭውውቱ መሃል ጓደኛሽ፣ ከባለቤትሽ ጋር ከመተዋወቃችሁ በፊት ጓደኛሽ ስለነበረ አንድ ሰው አነሳች። ከዚህ በፊት ይህን ታሪክ ለሴት ልጅሽ አልነገርሻትም። አሁን ልጅሽ ተጨማሪ ነገር ለማወቅ ፈልጋለች። ታዲያ ምን ታደርጊያለሽ?
አብዛኛውን ጊዜ የተሻለው ነገር ለልጅሽ ጥያቄ መልስ ለመስጠት መሞከር ነው። ልጅሽ ጥያቄ ጠይቃ የምትሰጫትን መልስ ስታዳምጥ የልባችሁን ለማውራት የሚያስችል አጋጣሚ ይከፈታል፤ ይህ ደግሞ አብዛኞቹ ወላጆች የሚፈልጉት ነገር ነው።
ታዲያ ለወንድ ልጅሽ ወይም ለሴት ልጅሽ ስለ ቀድሞ ሕይወትሽ መናገር የሚኖርብሽ ምን ያህል ነው? በአብዛኛው የሚያሳፍርሽን ነገር ከመናገር መቆጠብን ትመርጪ ይሆናል። ሆኖም ተገቢ በሚሆንበት ጊዜ፣ የፈጸምሻቸውን አንዳንድ ስህተቶችና አስቸጋሪ የሆኑብሽን ነገሮች ለልጆችሽ ብትነግሪያቸው ሊጠቅማቸው ይችላል። እንዴት?
አንድ ምሳሌ ተመልከቺ። በአንድ ወቅት ሐዋርያው ጳውሎስ “ትክክል የሆነውን ነገር ማድረግ ስፈልግ ከእኔ ጋር ያለው ግን መጥፎ ነገር ነው። . . . እኔ ምንኛ ጎስቋላ ሰው ነኝ!” ብሎ ስለራሱ ተናግሯል። (ሮም 7:21-24) ይሖዋ አምላክ እነዚህ ቃላት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንዲመዘገቡና እስከ ዛሬ ተጠብቀው እንዲቆዩ ያደረገው ለእኛ ጥቅም ሲል ነው። (2 ጢሞቴዎስ 3:16) በእርግጥም ደግሞ ጥቅም እናገኝበታለን፤ ምክንያቱም ሁላችንም ጳውሎስ በግልጽ የተናገረውን ሐሳብ እንጋራለን።
በተመሳሳይም ልጆችሽ አንቺ ስላደረግሻቸው ጥሩ ምርጫዎች ብቻ ሳይሆን ስለሠራሻቸው ስህተቶችም ጭምር መስማታቸው ስሜትሽን እንዲረዱልሽና ይበልጥ እንዲቀርቡሽ ሊረዳቸው ይችላል። እርግጥ ነው፣ አንቺ ያደግሽበት ዘመን ከአሁኑ የተለየ ነው። ይሁን እንጂ ዘመኑ ቢለወጥም የሰው ተፈጥሮም ሆነ የመጽሐፍ ቅዱስ መሠረታዊ ሥርዓቶች አልተለወጡም። (መዝሙር 119:144) ስላጋጠሙሽ ተፈታታኝ ሁኔታዎችና እነዚህን እንዴት እንደተወጣሻቸው በጉርምስና ዕድሜ ላይ ከሚገኙ ልጆችሽ ጋር መወያየትሽ እነሱም የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች እንዲያሸንፉ ሊረዳቸው ይችላል። ካመረን የተባለው ወጣት “አንተን የሚያጋጥሙህ ተፈታታኝ ሁኔታዎች በወላጆችህ ላይ ደርሰው እንደነበር ስታውቅ ወላጆችህም እንዳንተው እንደሆኑ እንድትገነዘብ ያደርግሃል” ሲል ተናግሯል። አክሎም “ሌላ ችግር ሲያጋጥምህ ‘ወላጆቼም ይህንን ችግር አሳልፈው ይሆን?’ ብለህ ታስባለህ” ብሏል።
ይሁንና የነገርሻቸው ታሪክ ሁሉ ምክር በመስጠት መደምደም አለበት ማለት እንዳልሆነ ልብ ማለት ያስፈልግሻል። እውነት ነው፣ በጉርምስና ዕድሜ ላይ የሚገኙ ልጆችሽ የተሳሳተ ድምዳሜ ላይ ይደርሳሉ ወይም እነሱም ተመሳሳይ ስህተት ቢፈጽሙ ምንም ማለት እንዳልሆነ አድርገው ያስባሉ ብለሽ ትሰጊ ይሆናል። ይሁን እንጂ ልጆችሽ ከውይይቱ እንዲያገኙ የፈለግሽውን ትምህርት ግልጽ ለማድረግ (“እናንተ ፈጽሞ እንዲህ ማድረግ የሌለባችሁ ለዚህ ነው”) ብለሽ ከማጠቃለል ይልቅ አንቺ ምን እንደሚሰማሽ ብቻ በአጭሩ ተናገሪ። (“ያኔ እንዲህ ዓይነት ነገር ባላደርግ ኖሮ ደስ ይለኝ ነበር፤ ምክንያቱም . . .”)
ልጆችሽ ምክር እየተሰጣቸው እንደሆነ ሳይሰማቸው ከአንቺ ተሞክሮ ጠቃሚ ትምህርት ማግኘት ይችላሉ። ኤፌሶን 6:4
“አንድ ጊዜ ለእናቴ ከሌሎች ክርስቲያኖች ጋር ከምሆን ይልቅ ትምህርት ቤት አብረውኝ ከሚማሩ ልጆች ጋር ስሆን እንደሚቀልለኝ ሳልደብቅ ነገርኳት። በቀጣዩ ቀን እናቴ የጻፈችውን ደብዳቤ ጠረጴዛዬ ላይ አገኘሁ። በደብዳቤው ላይ እሷም ከክርስቲያኖች መካከል ጓደኛ የሚሆናት ሰው እንዳጣች ይሰማት እንደነበረ ነገረችኝ። ከዚያም አብሯቸው ሆኖ የሚያበረታታቸው ሰው ሳይኖር አምላክን ስላገለገሉ ግለሰቦች የሚተርኩ የመጽሐፍ ቅዱስ ዘገባዎችን እንዳስታውስ አደረገችኝ። በተጨማሪም የሚያንጹ ጓደኞች ለማፍራት ስላደረግሁት ጥረትም አመሰገነችኝ። ይህ ችግር የገጠመኝ እኔ ብቻ አለመሆኔን ሳውቅ ገረመኝ። እናቴም እንደኔው ዓይነት ችግር ገጥሟት ነበር፤ ይህን በማወቄ በጣም ደስ ስላለኝ አለቀስኩ። እናቴ በነገረችኝ ነገር በጣም ተበረታታሁ፤ እንዲሁም ትክክል የሆነውን ነገር ለማድረግ ጥንካሬ አገኘሁ።”—የ17 ዓመቷ ንጹህ ፣
0 comments:
Post a Comment